Friday, January 31, 2014

የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ የዓለማችን 107ኛ ጠንካራ ሊግ ተባለ



    የዓለም አቀፉን እግር ኳስ ፌደሬሽንን ታሪክና ስታስቲክስ የሚመዘግበው ድርጅት አይ ኤፍ ኤፍ ኤች ኤስ /IFFHS/ .. 2013 ውጤት ተከትሎ ባወጣው ሪፖርት የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ በዓለማችን 107ኛው ጠንካራ ሊግ መሆኑን አሳውቋል፡፡

ድርጅቱ ደረጃውን የሚያወጣው የየሀገራቱ ክለቦች በሀገር ውስጥና በዓለም አቀፍ ውድድሮች በሚያስመዘግቡት ውጤት መሰረት ነው፡፡ የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ ባለፈው ዓመት ከተሰጠው የ110ኛ ደረጃ በዚህ ዓመት 3 ደረጃዎችን ማሻሻል ችሏል፡፡

የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ ደረጃ ከወጣላቸው ሀገራት 18ቱን በመብለጥ ነው የ107ኛ ደረጃ የተሰጠው፡፡ በድርጅቱ ሪፖርት መሰፈርት የስፔን ላሊጋ ቀዳሚውን ሲይዝ፣ የእንግሊዝ ፕሪምር ሊግ ደግሞ ተከታይ ደረጃን ይዟል፡፡ የጀርመን ፣ ጣሊያንና ብራዚል ሊግም በቀደም ተከተል ከ3-5ኛ ደረጃ ተሰጥቷቸዋል፡፡

ከአፍሪካ ሀገሮች በሊጋቸው  ቀዳሚ ስፍራ የተሰጣቸው ቱኒዚያ፣ ግብጽና ናይጀሪያ ናቸው፡፡ሩዋንዳ፣ ቶጎ፣ ሴኔጋልና ኡጋንዳ በቀደም ተከትል ደካማ ሊግ ያላቸው ሀገሮች በመባል ተቀምጠዋል፡፡

No comments:

Post a Comment