Saturday, September 24, 2022

ከ1ኛ ክፍል እስከ ዶክተርነት ሕልማቸውን ያሳኩ 16 አብሮ አደጎች….


የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ የጤና ሳይንስ ኮሌጅ ዘንድሮ በመጀመሪያ ዲግሪ ከሚያስመርቃቸው 250 ከሚበልጡ የህክምና ተማሪዎች ውስጥ 16 ከልጅነት ጀምሮ የሚተዋወቁ ወላይታ ሊቃ ከተባለ ትምህርት ቤት አብረው የመጡ ወጣቶች ናቸው፡፡

አብሮ አደገቹ ከለጋ እድሜያቸው አንስቶ ሀኪም የመሆን ልዩ ፍላጎት የነበራቸው ሲሆን ህልማቸውን እውን ለማድረግም አብሮ በማጥናት እና በመደጋገፍ ሲተጉ መቆየታቸውን ይገልጻሉ፡፡ የዚህ ትልማቸው መነሻ የጀመረውም ወላይታ ሊቃ በወላይታ ልማት ማህበር (ወልማ) በተቋቋመው ትምህርት ቤት ነው።

 16 ጓደኛማቾች መሃል አብዛኛዎቹ ከአንደኛ ክፍል ጀምሮ አብረው የተጓዙና ጠቂቶቹ ደግሞ ከአምሰተኛ ክፍል ተቀላቅለዋቸው እስከ 12 ክፍል ድረስ በትምህረፍት ቤቱ ቆይታ አድርገዋል። የወላይታ ሊቃ ትምህርት ቤት መምህራን ዛሬ ለደረስንበት ደረጃ የማይተካ ሚና ነበራቸው የሚሉት ሀኪሞቹ ግንኙነታቸው የተማሪ እና የአስተማሪ አይነት ሳይሆን የወላጅ እና የልጅ እንደነበረ ያስታውሳሉ። 

 


ወላይታ ሊቃ ትምህርት ቤት አቅም በፈቀደ በእውቀት የዳበረ እና ራዕይ ያለው የተማረ የሰው ኃይል ለማፍራት ከሚያደርገው ጥረት ባሻገር፣ ተማሪዎችን በመልካም ስብዕና ለማነፅ የነበረው ቁርጠኝነት ለዛሬ የተሟላ ስብዕናቸው መሠረት እንደነበርም አውስተዋል። 

 አብሮ አደገቹ ሐኪሞች ዩኒቨርስቲ ከገቡም በኋላ ግንኙነታቸው ይበልጥ ተጠናክሮ ያለፉትን 7 ዓመታት በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ የጥቁር አንበሳ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል በብርቱ ወንድማማችነት ያሳለፉ ሲሆን፣ በግቢ ቆይታቸውም የሕክምና ትምህርት የሚጠይቀውን ትዕግሥት እና ትጋት ማዳበራቸውን ለኢዜአ ተናግረዋል።

ብፁዕ አቡነ ኤርምያስ የክብር ዶክትሬታቸውን ከባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ ተቀበሉ።


 ባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ ተገኝተው በዩኒቨርሲቲው የተበረከተላቸውን የክብር ዶክትሬታቸውን ተቀብለዋል። ብፁዕነታቸው ለሐዋርያዊ አገልግሎት ከሀገር ውጭ ስለ ነበሩ የባህር ዳር ዩኒቨርሲቲ ነሐሴ 21 ቀን 2014 . የሰጣቸውን የክብር ዶክትሬት በአካል ተገኝተው መቀበል አልቻሉም ነበር፡፡

የክብር ዶክተር ብፁዕ አቡነ ኤርምያስ፥ አሸባሪው ሕወሓት ሰሜን ወሎን በወረራ ይዞ በነበረበት ወቅት ለተራቡት አብልተዋል፣ ለተጠሙት አጠጥተዋል፣ ለታረዙት አልብሰዋል፤ ያዘኑትን አጽናንተዋል። 5 ወራት በቆየው ወረራ የወልድያና አካባቢውን ሕዝብ ሃይማኖት፣ ዘር፣ ቋንቋ ሳይመርጡ ክፉ ቀንን አሳልፈዋል። በዚህም ወላዶች፣ ቁስለኞች፣ በችግር ላይ የነበሩ ወገኖች ከጉዳት ተርፈው መልካም ቀንን እንዲያዩ አድርገዋል። ይህ ስራቸውም የክብር ዶክትሬት እንዲያገኙ አስችሏቸዋል፡፡

ብፁዕ አቡነ ኤርምያስ (የክብር ዶክተር) በበኩላቸው "ሁሉ ከእርሱ፣ ሁሉ በእርሱ፣ ሁሉም ለእርሱ በመሆኑ የመከራው ቀን አልፏል፤ የተሰጠኝ የክብር ዶክትሬት ወገኑን ለማትረፍ መልካም ነገርን ሁሉ ላደረገ ሕዝብ ነው" ብለዋል። ብፁዕነታቸው በወቅቱ 5 ወራት እህል፣ ውኃ፣ ልብስ፣ መብራት በሌለበት ወቅት ችግር ላይ ወድቆ የነበረን ሕዝብ በእግዚአብሔር ድጋፍ ወደ ሰላም እንዲመለስ ማድረጋቸውን ተናግረዋል።

የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት / ፍሬው ተገኘ በበኩላቸው "ብዙዎች ከአካባቢያቸው በሚሸሹበት ወቅት በጦርነት ውስጥ ወደ ሚገኘው ሕዝባቸው በመሄድ የመከራ ቀን እንዲያልፍ ታሪክ የማይረሳው ሥራን ሠርተዋል" ብለዋል። በዚህም የከበረ ሥራን አከናውነው የከበሩትን በማክበራችን እኛም ብዙ አትርፈናል በማለት ገልጸዋል፡፡

ልጇ ክብር በማግኘቱ ቤተክርስቲያን ደስ ብሏታል ያሉት በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ እና የባሕር ዳር ሀገረ ስብከት ሊቀጳጳስ ብፁዕ አቡነ አብርሃም ናቸው። ከዲቁና እስከ ሊቀ ጵጵስና ድረስ በትክክል የበጎች እረኛ መሆናቸውን አረጋግጠዋል ሲሉም ምስክርነታቸውን ሰጥተዋል።

ከሀገር ውጭ የነበሩት ብፁዕ ኡቡነ ኤርምያስ ዛሬ ረፋዱን ወደ ባሕርዳር ሲገቡ ብፁዓን አባቶች፣ ሊቃውንት፣ የመንግስት ባለስልጣናት እና የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ ከፍተኛ አመራሮች በባሕር ዳር ዓለም አውሮፕላን ማረፊያ ተገኝተው አቀባበል ተደርጎላቸዋል። ባለፈው ነሐሴ 21/2014 . ባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ ለብፁዕ አቡነ ኤርምያስና ለኮማንደር አትሌት ደራርቱ ቱሉ የክብር ዶክትሬት መስጠቱ ይታወሳል።