Friday, January 31, 2014

ሴፕ ብላተር በደቡብ አፍሪካ የማንዴላን ቤተሰቦች ጎበኙ


 የቻን የፍጻሜ ጨዋታን ለመታደም ደቡብ አፍሪካ የተገኙት የዓለምአቀፉ እግር ኳስ ፌደሬሽን /ፊፋ/ ፕሬዝዳንት  ሴፕ ብላተር የማንዴላን ቤተሰቦች ዛሬ ጎበኙ፡፡  
     በጉብኝቱ የፊፋው ዋና ፀሀፊ ጀርሞ ቫልክ፣ የአፍሪካ እግር ኳስ ፌደሬሽን /ካፍ/ ፕሬዘዳንት ኢሳ ሀያቶ፣ የደቡብ አፍሪካው እግር ኳስ ፌደሬሽን ፕሬዘዳንት ዳኒ ጆርዳን እንዲሁም የተለያዩ የዘርፉ አካላት ተካፋይ ሆነዋል፡፡እዚህ የተገኘነው ዓለም ያጣችውን ታላቅ መሪ ቤተሰቦች ለማግኘትና ደጋፋችንን ለመግለጽ ነው ብለዋል ሴፕ ብላተር ፡፡ ጨምረውም ማንዴላ ለሰባዊ መብት የከፈለው መሰዋትነት በእኛ ታላቅ ክብር አለው ሲሉ ተናግረዋል፡፡

የማንዴላ ልጅ የሆነው ዚንዲ ፊፋ ለቤተሰቦቹ  እያደረገ ያለውን ደጋፍ በማመስገን፣ እግር ኳስ ህዝቦችን የማቀራረብ ሃይል ስላለው ለዓለም አቀፍ ሰበዊ እርዳታ እንቅስቃሴ  ልንጠቀምብት ይገባል ብሏል፡፡ ማንዴላ ለሰባዊ ተግባራት የከፈሉትን መሰዋትነት በማስታወስ፡፡
                                                    
                                                         ምንጭ ፡- ኢሬቴድ

No comments:

Post a Comment