Wednesday, April 10, 2013







  በኢትዮጵያ  በተለያዩ  የኢንቨስትመንት  ዘርፎች ላይ እየተንቀሳቀሰ የሚገኘው የቻይናው ጉአንግዶንግ ቹአን ግሩፕ የተባለው ኩባንያ  በመዲናችን በርዝመቱ ቀዳሚ የሆነ ህንፃን  ሊገነባ መሆኑን  ገልጿል
   ኩባንያው ያወጣው ጋዜጣዊ መግለጫ  እንደሚያስረዳው  በከተማዋ  ኡራኤል አካባቢ ለሚገነባውና ለሆቴል  ግልጋሎት  ለሚውለው ህንፃ  የሚሆን 41 ሺህ /ካሬ ሜትር  ቦታን ከከተማዋ አስተዳደር አግኝቷል  በዲዛይኑ  መሰረት  ህንፃው 99  ወለሎች ሲኖሩት  448 ሜትር  ከፍታም  እንዲኖረውም ነው የታቀደው
  ኩባንያው ከሶስተኛ እስከ 55  ፎቅ ያሉትን ክፍሎች ለቢሮ ግልጋሎት እንደሚውሉና  78  አስከ 94 ፎቅ የሚገኙትን ደግሞ  ባለ አምስት ኮከብ  ደረጃ  ያላቸው 217 የሆቴል  ክፍሎችን  እንደሚይዙ አስታውቋል  የኢትዮጵያ የቻይናና  የጣሊያን  ባህላዊ  የምግብ ዓይነቶችም  በህንፃው ላይ በሚገኙ አምስት ምግብ  ቤቶች ይዘጋጃሉ
  ህንፃው  የመኪና ማቆሚያዎች መናፈሻዎችንና  ቤተ መፅሃፍትንም  አካቶ የሚይዝ ይሆናል  ኩባንያው የህንፃውን ስም የቀድሞው ጠቅላይ  ሚኒስትር  መለስ ዜናዊን ለመዘከር በእርሳቸው ስም ለመሰየምም እቅድ አለኝ ብሏል

No comments:

Post a Comment