Sunday, April 21, 2013


ጸጋዬ ከበደ የለንደን ማራቶንን አሸነፈ



ሚያዚያ 13 ፣ 2005  በተካሄደው የለንደን ማራቶን ኢትዮጵያዊው ጸጋዬ ከበደ አሸነፈ።
ጸጋዬ በ2 ሰአት ከ6 ደቂቃ ከ03 ማይክሮ ሰከንድ ነው ውድድሩን በአንደኛነት ያጠናቀቀው።
ሌላው ኢትዮጵያዊ አየለ አብሽሮ ሶስተኛ ሆኖ ሲያጠናቅቅ  ፈይሳ ሌሊሳ  ውድድሩን አራተኛ ሆኖ አጠናቋል።
 
   ውድድሩን በአብዛኛው ሲመራ የቆየው ኬንያዊው ኢማኑኤል ሙታይ በሁለተኝነት ጨርሷል።


የሴቶቹን ውድድር ኬኒያዊቷ ፕሪስካ ጄፕቱ በአንደኛነት አጠናቃለች።  ይህ በእንዲህ እንዳለ የለንደን ኦሎምፒክ ባለወርቅ ሜዳሊያ የሆነችው ኢትዮጵያዊቷ ቲኪ ገላና  ፥ ጆሽ ኬስዲ ከተባለ ካናዳዊ የዊልቸር ተወዳዳሪ ጋር በመጋጨቷ ውድድሩን 16ኛ ሆና ነው ማጠናቀቅ የቻለችው  ።
እንኳን ደስ አለህ … ስለ አኮራህን የሀገራችንንም ስም ስላስጠራህ ከልብ እናመሰግናለን !

No comments:

Post a Comment