Thursday, June 17, 2021

“ከስነ ጥበብ ዘርፎች ሁሉ ለእኛ እጅግ አስፈላጊው የስነ ራዕይ ጥበብ ነው” - ሁለገብ የፊልም ባለሙያ ብርሃኑ ሽብሩ፡፡

የፊልም አዘጋጅ፣ ተዋናይ፣ ፀሃፊ እና መምህር ነው፡፡ ትምህርቱን በሀገር ውስጥ እና በውጪ ተምሯል፡፡ 12ኛ ክፍልን ጨርሶ የሙዚቃ ትምህርትን የተከታተለ ሲሆን በጊዜው ሜጀሩን “ባሱን” እና ማይነሩን ፒያኖ በማድረግ በከፍተኛ ማዕረግ ተመርቋል፡፡ በተለይ “ባሱን” በተባለው የሙዚቃ መሳሪያ በኢትዮጵያ የመጀመሪያው እንደሆነም ይነገርለታል፤ ሁለገብ የፊልም ባለሙያ ብርሃኑ ሽብሩ፡፡

በሙዚቃ ትምህርት በከፍተኛ ማዕረግ ከተመረቀ በኋላም ነፃ የትምህርት እድል አግኝቶ ወደ ቀድሞዋ ሶቬት ህብረት በማቅናት ለአንድ አመት ቋንቋ እና ስነ ፅሁፍ ተምሯል፡፡ ከዚያም የሲኒማ፣ የትያትር እና የቴሌቭዥን ስራዎች ዩኒቨርስቲ ውስጥ ለአንድ አመት ትያትር አመራር /ዳይሬክቲንግ/ እና ትወና አጥንቷል፡፡ በማስከተልም በፊልም ፋካሊቲ(ትምህርት ክፍል) የልብ ወለድ ፊልም ትወና ጥበብን ለ5 አመት ተምሯል፡፡ በትምህርት ቆይታውም 9 ያህል ፊልሞችን እና 6 ያህል ተውኔቶችን ከተለያዩ ሀገራት የትምህርት አጋሮቹ እና የፊልም ባለሙያዎች ጋር ሰርቷል፡፡ ለአብነትም የሰው ያለህ፣ የመጨረሻው ውይይት፣ ፀሀይ ስትጠልቅ፣ የትም ምንም አለ(Nothing is everywhere) ፣ የቀረ መንገደኛ እና ነፍሰ ገዳይ ከብዙ በጥቂቱ ይጠቀሳሉ፡፡


ትምህርቱን ጨርሶ ወደ ኢትዮጵያ ከተመለሰ በኋላም የኢትዮጵያ ፊልም ኮርፖሬሽንን በመቀላቀል የተለያዩ ስራዎችን ሰርቷል፡፡ በአጠቃላይ በግል እና በጋራ 70 የሚደርሱ ሰራዎችን ሰርቷል፡፡ በተለያየ መንገድ ከተሳተፈባቸው የፊልም ፣ ድራማ እና ቪዲዮ ስራዎቹ መካከል፡-

 - የተስፋ ጉዞ                  - እናት አርሲ        - ተስፋ አልባ ወጣቶች

- በህይወት ዙሪያ               - ኑረት           - ግልፅ የመሆን ጊዜ 

- ዋስትና - የሰላም ባዳነት       - የሞት ፍቅር        - ማናት

- ኮንሶ ካራት                  - የጊዜያችን ሰዎች     - ውስጠት

- ንቅዘት                      - ጎዳና                - ሰባራ መስተዋት

-  የሞት ሸለቆ           - የወፍ ጎጆ          - ሀድጊ የትግሪኛ የቴሌቭዥን ድራማ(ዳይሬክት በማድረግ)

- ገበና ቁጥር 1 (በትወና) የመሳሰሉትን ማነሳሳት ይቻላል፡፡ በተለይ ገበና ቁጥር 1 የፍሰሃ ገፀ ባህሪን ወክሎ ከጀማነሽ ሰለሞን (በድራማ ገፀ ባህሪዋ - ማርታ ጋር) ባሳየው የትወና ብቃት በብዙዎች ዘንድ ይታወቃል፡፡ በዚህ የቴሌቭዥን ድራማ ምክንያት በተለያየ ጊዜ ያገኙትን 12ሺ አድናቂዎቹን ስም የመዘገበ ሲሆን በግለሰቦቹ ስም በአንድ ሰዓሊና ቀራፂ እመቤት በለጠ አማካኝነት ስዕል ተሰርቶ ለኤግዚብሽን ቀርቦም ነበር፡፡ ከዳይሬክቲንግ ፣ ትወና እና መምህርነት ባሻገር የተለያየ አርቲክል እና ግጥሞችን በመፃፍም ይታወቃል፡፡ የጉማ ፊልም ሽልማት ላይም በማማከር እና በዳኝነት ሰርቷል፡፡ 

በአጠቃላይ በተማረው ትምህርት እና ባገኘው ልምድ የሀገራችንን የፊልም ኢንዱስትሪ ለማሳደግ የበኩሉን አስተዋፅኦ እያበረከተ ይገኛል፡፡ ስለ ሁለገቡ የፊልም ባለሙያ ብርሃኑ ሽብሩ ከብዙ በጥቂቱ  እኔ ይህንን አልኩ ፣ እናንተ ደግሞ ያላችሁን ሀሳብ እና አስተያየት አጋሩኝ፡፡ ለእንግዳዬ ብርሃኑ ሽብሩ እድሜ ከጤናና ስራን ከስኬት ጋር እመኛለሁ!!!

Wednesday, March 10, 2021

ድምፃዊት እና ተዋናይት ዘቢባ ግርማ - ገራገር …!!!


ገራገር  ያማል ቅኔው አዲስ ፍቅር የተሰኙት ዘፈኖች ከተወዳጅ ስራዎቿ መካከል ይጠቀሳሉ፡፡ ለማን ብዬ ፍቅር ይብዛ አበባየሆ ጣይቱ እና ሌሎች ሙዚቃዎችን በግል እና በጋራ ተጫውታለች፡፡ በተለይ ገራገር በአንድ ቀን ውስጥ 500,000 በላይ የዩቲዩብ እይታ በማግኘት ሪከርድም ይዞ ነበር፡፡ ከድምፃዊነቷ ባሻገርም የእኛዎቹን በመቀላቀል በሬዲዮ ድራማ እሙዬን ገፀ ባህሪ በኋላም ምን ልታዘዝ የተሰኘ የቴሌቭዥን ድራማ ላይ ደግሞ የንጉስ ነሽን ገፀ ባህሪ ወክላ በመጨዋት ተወዳጅነትን አትርፋለች፤ ድምፃዊት እና ተዋናይ ዘቢባ ግርማ፡፡


ከትምህርት ቤት የጀመረው የሙዚቃ ፍላጎት እና ተስጥኦ በብዙ ውጣውረዶች ውስጥ አልፋ አሁን ላለችበት ደረጃ ደርሳለች፡፡ ተማሪ እያለችም በት/ቤቶች መካከል በሚደረግ የሙዚቃ ውድድር በመሳተፍ አንደኛ አንደኛ እየወጣች የተለያዩ ሽልማቶችን አግኝታለች፡፡ የሸገር ሬዲዮ የድምፃውያን ውድድር ላይ 3 ወጥታ ብታሸንፍም በኢትዮጵያ አይዶል ውድድር ግን 3 ዙር መሻገር አልቻለችም ነበር፡፡

ከክቡር / ተስፋዬ አበበ የጥበብ ማዕከል የኛዎቹ የተመረጠችው ዘቢባ በቡድኑ ውስጥ 5ሴት እና 1 ወንድ ሆነው የተለያ የሙዚቃ የሬዲዮ ድራማ እና የሙዚቃ ኮንሰርቶችን በመስራት በጋራ 8 አመታት አብረው ዘልቀዋል፡፡ በዚህ ቆያታቸውም 40 ያህል ሙዚቃዎችን ሰርተዋል፡፡ ከየኛዎቹ ወደ እንደኛ የሙዚቃ ቡድን ቢመጡም አሁን ላይ ከቡድን ስራቸው ይበልጥ በየግል በሚሰሯቸው ስራዎች ውጤታማ እየሆኑ ነው፡፡


በስራዎቿ ተወዳጅነትን ያተረፈችው ድምፃዊት እና ተዋናይ ዘቢባ ግርማ በሀገር ውስጥ እና በውጪ የተለያ አካባቢዎች ስራዎቿን አቅርባለች፣ እያቀረበችም ነው፡፡ በቀጣይም በአልበም ለመምጣት እንዳሰበች ጠቆም አድርጋናለች፡፡ ዘቢብ ጅማሬሽ ጥሩ ነውና ፍፃሜሽም እንዲያምር መልካሙን ሁል እንመኝልሻለን፡፡

 

Wednesday, February 10, 2021

ያልተዘመረለት ባለሙያ …. አርቲስት ዘላለም መኩሪያ


የዘፈን ግጥም እና ዜማ ደራሲ አሳታሚ እና አከፋፋይ እንዲሁም የቀድሞ ኢትዮጵያ አይዶል እና የኮካ ኮላ ሱፐር ስታር ዳኛ ነው  የአስጎብኚ ድርጅት ከፍቶም እየሰራ ይገኛል፤ ሁለገቡ ባለሙያ ዘላለም መኩሪያ፡፡

ስለ ስራዎቹ በጥቂቱ እነሆ.

              # በግጥም እና ዜማ ደርሰት:-

1. መሀሙድ አህመድ - ብክንክንመውደድ አዛዥ ነው

2. አለማየሁ እሸቴ - ደገኛ ነችልሂድ ልወዝወዘው

3. ኤፍሬም ታምሩ - አደላድዬውእስከ መቼም አልረሳውመውደድ/ፍቅር በኔ ፀንቶ

4. ፀጋዬ እሽቱ - ክፉ አልምደሽኝ/እናት ወደር የላት/

5. አረጋኽኝ ወራሽ - የአምባው ዳኛ

6. ኬኔዲ መንገሻ - ዘወርዋራ (የመጀመሪያ ስራው ነው)

7. ሰርጉአለም ተገኝ - በምን ቃል አሆበል

8. ማዲንጎ አፈወርቅ - አይደረግምስያሜ አጣሁላት

9. በዛወርቅ አስፋው - መውደድ ካኮራህ /ልቤን ታዘብኩት/

10. ማርታ አሻጋሪ - እምቢ እምቢ ፣ ግልፅ ነው ስሜቴ ፣ የልጅ ነገርማ እና ሌሎችም በዛ ያሉት የእሱ ስራዎች ናቸው፡፡

11. ተሾመ አሰግድ - እረ እንዲያው በረታ

12. ውብሸት ፍሰሃ - መካር የላት ምነው

13. ነፃነት መለሰ- ያለስንብትያይኔራብ ይወስደኛል

14. ኩኩ ሰብስቤ - አከራርመኝ - ከውብሽት ጋር በመሆን

15. ሀይልዬ ታደሰ - አንቺን ይዞ (አንቺ የሌለሽበት)

16. ገረመው አስፋ - በይ እንዳሻሽ

17. ዳዊት መለሰ

18. ፋሲካ ዲመትሪ -

19. ኤልሳቤጥ ተሾመ - እፈራለሁ

20. ለኢትዮጵያ አይዶል ተወዳዳሪዎች (ለዳንኤል እና ሱራፌል)

 

               # በዜማ ድርሰት የተሳተፈባቸው የባህል ስራዎች

1. ታደሰ አለሙ - ሚሻ ሚሾ

2. የሺመቤት ዱባለ - አሳበለው (አልበም)

3. የኔጌጥ ፋንታሁን - ምን ይላል ጎንደር ሲከፋው : የልቤ ሌባ ቀማኛ (የዳኛ ዳኛ)

 4. መሰሉ ፋንታሁን - አይንዬ

 5. ማናሊሞሽ ዲቦ - አሳበለውአለሁ በለኝ

 6. እያዩ ማንያዝዋል - ከብዙ በጥቂቱ የእሱን የዜማ እና ግጥም ድርሰቶች የተጫወቱ ድምፃውያን ናቸው፡፡

               # ህብረ ዜማዎች

- የመከላከያ ሰራዊት መዝሙርየአፍሪካ ህብረትየኮፒ ራይት - (ይስማን ወገን ይስማን) የኢትዮጵያ አይዶል አሸናፊዎችየኤፍ ኤም አዲስ 97.1  ፣ የአርበኞች በዓልለአትሌቶች - የሲድኒው ሰራዊት እና የደል ብስራት (ለመከላከያ የተሰራ) ጥቂቶቹ ናቸው፡፡


                                 # በሙዚቃ ህትመት እና ማከፋፈል ደግሞ

  1. አሳበለው - መሰሉማናሊሞሽ እና የኔጌጥ

  2. ስያሜ አጣሁላት - ማዲንጎ አፈወርቅ

  3. እድሜዬን በሙሉ - አብርሽ ዘጌት

  4. ባንቺው መጀን - ደርብ ዘነብ

  5. የኔ ድሃ - ነዋይ ደበበ

  6. ሰም እና ወርቅ - ጂጂ(እጅጋየሁ ሽባባው)

  7. ባስረሳኝ - ብፅአት ስዩም

  8. የሰላም ይሁን - አስፋው ፅጌ

 9. ሚሻ ሚሾ - ታደሰ አለሙእነዚህና ሌሎች ስራዎችን በማሳተም በሙዚቃው ውስጥ አሻራውን አኑሯል፡፡

   በኢትዮጵያ አይዶል እና ኮካ ኮላ ሱፐር ስታር የተስጥኦ ውድድርን በዳኝነት መርቷል፡፡ ልዩ ልዩ በዓላትን እና ሌሎች ስራዎችን ከቴሌቭዥን ጣቢያዎች ጋር በትብብር እየሰራ ይገኛል፡፡ በተጨማሪም የአስጎብኚ ድርጅት ከፍቶ ዜጎችን ወደ እየሩሳሌም በመውሰድ ያስጎበኛል፡፡ ስለ ሁለገቡ የጥበብ ሰው ዘላለም መኩሪያ ብዙ ማለት ቢቻልም እኔ ግን እዚህ ላይ አበቃለሁ፡፡ በተረፈ እናንተ ጨምሩበት....