Thursday, April 25, 2013



  በወላይታ ሶዶ 4.0 የተለካ የመሬት መንቀጥቀጥ ተከሰተ

   

    ሚያዚያ ፣ 16 ፣ 2005  በትናንትናው ዕለት በወላይታ ሶዶ ከተማና አካባቢዋ ላይ የተከሰተው ቀላል የመሬት መንቀጥቀጥ በሰውም ሆነ በንብረት ላይ ምንም አደጋ እንዳላደረሰ የወላይታ ዞን ባህል ቱሪዝም መንግስት ኮሚዩኒኬሽን ቢሮ አስታወቀ።

    የቢሮው አስተባባሪ አቶ አብርሃም ኦቾሬ እንዳሉት የመሬት መንቀጥቀጡ በሬክተር ስኬል 4.0 የተመዘገበ ነው።

  
     የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የጂኦ ፊዚክስ ባለሙያ የሆኑት ዶክተር አታላይ አየለ  መሰል የመሬት መንቀጥቀጥ አደጋ በሰምጥ ሸለቆ አካባቢ ባሉ ከተሞች ላይ አልፎ አልፎ የሚከሰት ነው ብለዋል። ይህ በመሆኑም በአካባቢዎቹ የሚገነቡ ሀንጻዎች ላይ ተገቢው ጥንቃቄ ሊደረግ እንደሚገባ አሳስበዋል።

No comments:

Post a Comment