Thursday, June 27, 2013

ኢትዮጵያዊያን አትሌቶች በአውሮፓ መድረኮች የበላይነታቸውን አሳዩ

ባለድሎቹ መሀመድ፣ ጥሩነሽ፣ መሰረት እና ደጀን
ባለድሎቹ መሀመድ፣ ጥሩነሽ፣ መሰረት እና ደጀን
ቼክ ሪፐብሊክ ኦስትራቫ ውስጥ (ሰኔ 27 ቀን 2013 ) በተካሄደው የሴቶች 10 ሺህ ሜትር የርቀቱ ንግስት ጥሩነሽ ዲባባ 30 ደቂቃ ከ26.67 ሰከንድ በሆነ ጊዜ በማጠናቀቅ እ.አ.አ ከ2008 ጀምሮ በርቀቱ በራሷ ተይዞ ቆይቶ የነበረው የስፍራውን ክብረወሰን አሻሽላ አሸንፋለች።
       ጥሩነሽ 10 ሺህ ሜትርን መሮጥ ከጀመረችበት ከስምንት አመት በፊት ጀምሮ አንድም ጊዜ ያልተሸነፈች ሲሆን ይህ የኦስትራቫ ድሏ 10ኛው ተከታታይ ድሏ ነው። በዚህ ውድድር ሌላዋ ኢትዮጵያዊት በላይነሽ ኦልጂራ ለራሷ የውድድር አመቱ ምርጥ ሆኖ በተመዘገበ ሰአት 30:31.44 በመጨረስ ኬኒያዊቷ ግላዴስ ቼሬኖን ተከትላ ሶስተኛ ደረጃን አግኝታ አጠናቃለች።

      ሌላው የኦስትራቫ የመሮጫ ትራክን ያደመቀ ኢትዮጵያዊ አትሌት የ800 ሜትር ኮከቡ መሀመድ አማን ሲሆን ርቀቱ ሊጠናቀቅ 60 ሜትሮች ያህል ሲቀሩት ባሳየው አስደናቂ የአጨራረስ ብቃት 1:43.78 በሆነ ጊዜ አሸናፊ ሆኗል። በርቀቱ የአለም የቤት ውስጥ ሻምፒዮን የሆነው መሀመድ አማን ራሱን የፊታችን ነሀሴ ወር በሞስኮ አስተናጋጅነት ለሚካሄደው የአለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና በግሩም ሁኔታ እያዘጋጀ ነው። ሞስኮ ላይ የመሀመድ አማን ቁጥር አንድ ተፎካካሪ እንደሚሆን የሚጠበቀው ኬኒያዊው የርቀቱ ንጉስ ዴቪድ ሩዲሻ በአሁኑ ጊዜ ጉዳት ላይ ነው።

      እንደገና በታደሰው የኦስታራቫው ሜስቲስኪ ስታዲዬም የተገኘው ተመልካች እ.አ.አ በ2004  በዚሁ ስታዲዬም በ10 ሺህ ሜትር የአለም ክብረወሰንን የሰበረው ታላቁ ቀነኒሳ በቀለ አስደናቂ ብቃቱን በ5 ሺህ ሜትርም ያሳያል በሚል ጠብቆ የነበረ ቢሆንም አስደናቂ ብቃቱን ለማሳየት የቻለው ሌላው ኢትዮጵያዊ ወጣቱ ሙክታር ኢድሪስ ነበር።
በርቀቱ የአለም ወጣቶች ሻምፒዮን ሙክታር በአስደናቂ የአጨራረስ ብቃት ርቀቱን በ13፡03.69 በማጠናቀቅ የራሱን ምርጥ ሰአት አስመዝግቦ አሸንፏል። ለአሸናፊነት ተጠብቆ የነበረው እና በርቀቱ የኦሎምፒክ እና የአለም ሻምፒዮን እንዲሁም የክብረወሰኑ ባለቤት የሆነው ቀነኒሳ በቀለ በኦስትራቫው ውድድር ርቀቱ ሊጠናቀቅ 400 ሜትሮች ያህል እስኪቀሩት ድረስ ከመሪዎቹ ጋር አብሮ የነበረ ቢሆንም ድሮ ይታወቅበት የነበረው ፍጥነት የመቀየር እና የአጨራረስ ብቃቱ አብሮት ባለመኖሩ 5 ሺህ ሜትሩን በ13፡07.88 አጠናቆ አራተኛ ደረጃን አግኝቶ ጨርሷል። ኬኒያዊያኖቹ አጉስቲን ቾጊ እና ላዊ ላላንግ እንደ ቅደም ተከተላቸው ሁለተኛ እና ሶስተኛ ደረጃን አግኝተው አጠናቀዋል።

   በሴቶች 3 ሺህ ሜትር መሰናክል ኢትዮጵያዊቷ ህይወት አያሌው ለራሷ ፈጣን የውድድር አመቱ ሰአት ሆኖ በተመዘገበላት 9:19.87 ጊዜ በማጠናቀቅ ሁለተኛ ሆና ጨርሳለች። የውድድሩ አሸናፊ ኬኒያዊቷ ሚልካ ቼሞስ ነች።

      ስዊድን ሶሌንቱና ውስጥ በተካሄዱት የአትሌቲክስ ውድድሮች (ሰኔ 27 ቀን 2013) በአብዛኛው በ5 ሺህ ሜትር የምትታወቀው ኢትዮጵያዊቷ ድንቅ የረጅም ርቀት ሯጭ መሰረት ደፋር በ10 ሺህ ሜትር ተወዳድራ ርቀቱን በ30፡08.06 በማጠናቀቅ ጥሩነሽ ዲባባ ኦስትራቫ ላይ ጥቂት ሰአታት ቀደም ብላ አስመዝግባው የነበረውን የአመቱን ፈጣን ሰአት በማሻሻል አስደናቂ ድል ተጎናጽፋለች።
      በርቀቱ የተካፈሉት ኢትዮጵያዊያኖቹ አፈረ ጎድፋይ (31፡08.23) እና ጎተይቶም ገብረስላሴ (31:51.42) የራሳቸውን ምርጥ ሰአት በማስመዝገብ መሰረትን ተከትለው ሁለተኛ እና ሶስተኛ ደረጃን አግኝተው አጠናቀዋል።

   ልክ እንደመሰረት ሁሉ ስዊድን ሶሌንቱና ውስጥ የነገሰው ኢትዮጵያዊው ደጀን ገብረመስቀል ሲሆን፣ በለንደን ኦሎምፒክ በ5 ሺህ ሜትር የብር ሜዳሊያ ባለቤት የሆነው ደጀን በ10 ሺህ ሜትር ተወዳድሮ ርቀቱን በ26:51.02 በማጠናቀቅ የአመቱን ፈጣን ሰአት በማስመዝገብ አስደናቂ ድል አግኝቷል። ከደጀን ጋር በ10 ሺህ ሜትሩ የተፎካከሩት ሌሎቹ ኢትዮጵያዊያን አበራ ኩማ በ26:52.85 የራሱን ፈጣን ሰአት እና የማነ መርጋ በ26:57.33 የራሱን የውድድር አመቱ ፈጣን ሰአት በማሻሻል እንደ ቅደም ተከተላቸው ሁለተኛ እና ሶስተኛ ደረጃዎችን አግኝተው አጠናቀዋል።

                                                                                          Source :- Total 433

Wednesday, June 19, 2013

ብሔራዊ ቡድኑ 3 ነጥብ ጎልና 6 ሺ የስዊስ ፈራንክ ይቀጣል

 የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ተገቢ ያልሆነ ተጫዋች በማሰለፉ የሚቀጣው 3 ነጥብ ጎልና 6000 የስዊስ ፈራንክ ብቻ መሆኑን የኢትዮጰያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን አስታወቀ፡፡

   ቦትስዋና ከኢትዮጵያ ባደረገችው ጨዋታ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡደን 2 ለ 1 ያሸነፈበት ውጤት ብቻ እንደሚሰረዝና 3 ነጥብ ለቦትስዋና እንደሚሰጥ የፊፋ ዲሲፕሊን ኮሚቴ ማሳወቁን የኢትዮጰያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን አረጋግጧል፡፡

    ስለሆነም ኢትዮጵያ ደቡብ አፍሪካን 2 ለ 1 ያሸነፈችበት ውጤት የሚፀና ሲሆን የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ምድቡን በ10 ነጥብ እየመራ የሴንትራል አፍሪካውን ጨዋታ ይጠባበቃል፡፡በዚህ መሰረትም ኢትዮጵያ በ10 ነጥብና 2 ንፁህ ጎል ስትመራ ደቡብ አፍሪካ በ8 ነጥብና 4 ንፁህ ጎል ትከተላለች፡፡ ቦትስዋና በ7 ነጥብና ያለምንም ግብ ክፍያ 3ኛ ስትሆን ማዕከላዊ አፍሪካ በ3 ነጥብ 6 የግብ እዳ በመጨረሻው ደረጃ ላይ ትገኛለች፡፡

Tuesday, June 18, 2013

     ፌዴሬሽኑ የፊፋን ክስ አመነ


       የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ምንያህል ተሾመ ሰኔ 1 ቀን 2005 ዓ.ም ከቦትስዋና ብሄራዊ ቡድን ጋር በተደረገው ጨዋታ መሰለፉ ስህተት እንደሆነ አመነ፡፡

    ፌዴሬሽኑ ብሄራዊ ቡድኑ ከደቡብ አፍሪካ  አቻው ጋር ከመጫወቱ በፊት ችግር ስለመፈጠሩ ከፊፋ ደብዳቤ ደርሶት እንደነበርም ገልጿል፡፡ ተጫዋቹ መጫወት እንደማይችል ከ18 ቀን በፊት መረጃ ቢደርሰውም ተግባራዊ አላደረገም፡፡

    የፌዴሬሽኑ የስራ አስፈፃሚ ኮሚቴ ለችግሩ ተጠያቂ ያላቸውን ግለሰቦች ዝርዝርም ይፋ አድርጓል፡፡ በዚህ መሰረት የብሄራዊ ቡድኑ ቡድን መሪ አቶ ብርሀኑ ከበደ ፣ አሰልጣኝ ሰውነት ቢሻው ፣ ረዳት አሰልጣኝ ስዩም ከበደ ፣ የቡድኑ ተጨዋች ምንያህል ተሾመ እና የፌዴሬሽኑ ፅህፈት ቤት ኃላፊዎች ጥፋተኛ ተብለዋል። ስራ አስፈፃሚ ኮሚቴው በጥፋተኞቹ ላይ በቅርቡ ተገቢውን ቅጣት በመውሰድ የቅጣት ውሳኔውን ለህዝብ ይፋ እንደሚያደርግ አስታውቋል፡፡

         ፌዴሬሽኑ በተፈጠረው ችግር ከፍተኛ ሀዘን እንደተሰማው ገልፆ መላውን የኢትዮጵያ ህዝብ ይቅርታ ጠይቋል፡፡ የቡድኑ አሰልጣኝ ሰውነት ቢሻው በተፈጠረው ስህተት የተሰማቸውን ሀዘን ገልፀው ፥ ከማዕከላዊ አፍሪካ ሪፐብሊክ ጋር ለሚካሄደው ጨዋታ ከወዲሁ መዘጋጀት እንደሚገባ ተናግረዋል፡፡

     በጨዋታውም አሸንፈን ወደ አለም ዋንጫ እንደምንሳተፍ እርግጠኛ ነኝ ብለዋል አሰልጣኙ፡፡
በፊፋ ህግ መሰረት ተገቢ ያልሆነ ተጨዋችን ማሰለፍ በጨዋታው የተገኘውን ነጥብ እና ተጨማሪ የገንዘብ ቅጣትም ያስጥላል፡፡

የኢትዮጵያ የአረንጓዴ ኢኮኖሚ ፖሊሲ ለአፍሪካ ሀገራት አርአያ ይሆናል

የኢትዮጵያ የአረንጓዴ ኢኮኖሚ ፖሊሲ  ለአፍሪካ ሀገራት አርአያ ይሆናል
     በኢትዮጵያ እየተተገበረ ያለው የአረንጓዴ ኢኮኖሚ ለሌሎች የአፍሪካ ሀገራት በአርአያነት የሚጠቀስ መሆኑን የአፍሪካ ሃይል አቅርቦት ጉዳዮች ማህበር ገለፀ፡፡

     በአለም አቀፍ የሃይል ካውንስል፣ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ሀይል ኮሚቴ፣ የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን እና የአፍሪካ ሀይል አቅርቦት ማህበር ቀጣይነት ያለው የሀይል አቅርቦት ለአፍሪካ“ በሚል መሪ ሀሳብ ያዘጋጁት አውደ ጥናት በአዲስ አበባ ተጀምሯል፡፡ በአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን የመሰረተ ልማት እና ሀይል ዳይሬክተር ዶክተር አቡበከር ባባ ሙሳ አፍሪካ አሁን ያለችበትን ፈጣን የዕድገት ጉዞ ቀጣይነት እንዲኖረው የሀይል ልማት ዘርፍ ላይ ትኩረት ተሰጠቶ ሊሰራ ይገባል ብለዋል፡፡
 
   “የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን በተለይ በመሰረተ ልማት ዕድገት ለአፍሪካ  መርሀ ግብር 40 በመቶውን ለሀይል ልማት ዘርፍ ትኩረቱን ሰጥቶ ይሰራል፡፡በተለይም በንፋስ ፣ የውሃ  እና የፀሃይ ሃይል ማመንጫዎች ላይ በሰፊው ለመስራት ተዘጋጅቷል፡፡“

     የአፍሪካ ታዳሽ ሀይል አጠቃቀም ከሌሎች አሀጉሮች ጋር ሲነፃፀር ዝቅተኛ መሆኑን እና በታዳሽ የሃይል ልማት ዘርፍ ላይ የተጠናከረ ስራ ሊሰራ እንደሚገባም የአለም አቀፍ የሀይል ካውንስል የፕሮግራሞች ዳይሬክተር ኤሌና ኒኬሽ ገልፀዋል፡፡ የውሃ እና ኢነርጂ ሚኒስትር ዴኤታ አቶ ከበደ ገርባ በአለም ላይ በተከሰተው የአየር ንብረት ለውጥ ችግር ኢትዮጵያም ተጎጂ በመሆንዋ በተለይም ለታዳሽ ሀይል ልማት ትኩረት እንደተሰጠው ገልፀዋል፡፡የአፍሪካ ሀይል አቅርቦት ማህበር ዋና ሃላፊ በበኩላቸው የኢትዮጵያ የአረንጓዴ ኢኮኖሚ ፖሊሲ ለሌሎች የአፍሪካ ሀገራት በአርአያነት ይጠቀሳል ብለዋል፡፡

   “በእርግጥ በአፍሪካ በታዳሽ ሃይል አቅርቦት በኩል የተሰራው ስራ ዝቅተኛ ቢሆንም የኢትዮጵያ የአረንጓዴ ኢኮኖሚ ፖሊሲ ለታዳሽ ሀይል አቅርቦት ላይ ትኩረት ማድረጉ ለሌሎች የአፍሪካ ሀገራት ኢትዮጵያ እንደማሳያ ማድረግ እንችላለን፡፡ ”

     በአለም ላይ ባሉ ዘጠና ሀገራት እስከ 3 ሺ አባል ድርጅቶች ያሉት የአለም አቀፍ የሀይል  ካውንስል ፍትሀዊነት ያለው፣ ተደራሽ የሆነና ከአከባቢ ብክለት ነፃ የሆነ የሀይል አቅርቦትን ሁሉንም ተጠቀሚ ለማድረግ የተቋቋመ ድርጅት ነው፡፡

በኦስሎ የዳይመንድ ሊግ ውደድር መሰረት ደፋር በ5 ሺ ሜትር አሸነፈች

      በኖዌይ ኦስሎ የዳይመንድ ሊግ ውደድር መሰረተ ደፋር በ5 ሺ ሜትር አሸነፈች፡፡
የመሰረት ደፋር እና ገንዘቤ ዲባባን ፉክክር ጨምሮ 5 ኢትዮጵያውያን ያሳተፈው የ5 ሺ ሜትር በመሰረት የበላይነት ተጠናቋል፡፡

    መሰረት የገባችበት 14፡26፡90 የአመቱ ፈጣን ሰአት ሆኗል፡፡ በዚህም  መሰረት ደፋር በ 6 ነጥብ የዳይመንድ ሊግ የ5 ሺ ሜትር ፉክክሩን  በአንደኝነት መምራት ጀምራለች፡፡ገንዘቤ ዲባባ 3ኛ ደረጃን በመያዝ ውድድሩን አጠናቃለች፡፡ ኬንያዊቷ ቪዬላ ጂላጋት 2ኛ ወጥታለች፡፡
ቡዜ ድሪባ 6ኛ፣ ገነት ያለው 12፣ጎይቶቶም ገብረስላሴ 13ኛ ደረጃን በመያዝ ውድድራቸውን አጠናቀዋል፡፡

      በ8 መቶ ሜትር ከረጅም ጊዜ ጉዳት በኋላ ወደ ወድድር የተመለሰቸው ፋንቱ መረሶ 4ኛ ደረጃን በመያዝ ፈፅማለች፡፡ በ1ሺ 5 መቶ ሜትር ሴቶች አክሱማይት አምባዬ 2ኛ በመሆን ውድድሩን አጠናቃለች፡፡ ስዊዲናዊቷ ምእራፍ ባህታ  በርቀቱ ቀዳሚ ሆናለች፡፡ በ3ሺ ሜትር መሰናክል ሮባ ጋሪ 7 ኛ ሆኗል፡፡ኪፕራቶ በርቀቱ አሸንፏል፡፡በ 2 መቶ ሜትር ዩዚየን ቦልት 19፡79፡60 ሰዓት በመግባት የቦታውን እና የአመቱን ፈጣን ሰዓት በማሻሻል አሸንፏል፡፡
ቀጣይ የዳይመንድ ሊግ ፉክክር በእንግሊዝ በርማንግሀም ይካሄዳል፡፡

Monday, June 17, 2013

    ፊፋ ኢትዮጵያን ጨምሮ በቶጎ እና ኢኳቶሪያል ጊኒ ላይ ተመሳሳይ ምርመራ ከፈተ
 
   
    የኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድን ከዚህ ውጤት በኋላ ምድቡን አንድን በ13 ነጥብ በመምራት አንድ የምድብ ጨዋታ እየቀረ በጥሎማለፍ መልክ ወደሚካሄደው የቀጣዪ ዙር የአለም ዋንጫ ማጣሪያ ማለፏን ቢያረጋግጥም የአለም አቀፉ እግርኳስ ፌዴሬሽን ፊፋ እሁድ ማምሻውን ባወጣው ዜና “የኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድን በአለፈው ሳምንት ቦትስዋናን 2 ለ 1 በረታበት ጨዋታ ላይ ተሰልፎ መጫወት ያልነበረበት ተጨዋች አሰልፎ አጫውቷል” በሚል ምርመራ እንደሚደረግበት ማስታወቁ በኢትዮጵያዊያን ላይ የተፈጠረውን ታላቅ የደስታ ስሜት አደብዝዞታል።
 
    ፊፋ ኢትዮጵያን ጨምሮ በቶጎ እና ኢኳቶሪያል ጊኒ ላይ ተመሳሳይ ምርመራ የከፈተው የፊፋ የውድድር እና ስነ-ስርአት መተዳደሪያ ደንብ አንቀጽ 55 እና የብራዚሉ አለም ዋንጫ ማጣሪያ መተዳደሪያ ደንብ ላይ አንቀጽ ስምንትን በመጥቀስ ነው። የፊፋ የጨዋታ መዝገቦች እንደሚያሳዩት ከሆነ ምን አልባት መጫወት ሳይኖርበት የተጫወተው ምንያህል ተሾመ ሲሆን፣ ኢትዮጵያ ከደቡብ አፍሪካ ጋር 1 ለ 1 በተለያየችበት እና አዲስ አበባ ላይ ቦትስዋናን 1 ለ 0 በረታችበት ጨዋታዎች ላይ የቢጫ ማስጠንቀቂያ ካርዶች ያየ በመሆኑ በአለፈው ሳምንት ኢትዮጵያ ወደ ሎባትሴ አቅንታ ቦትስዋናን 2 ለ 1 በረታችበት ጨዋታ መሰለፍ አልነበረበትም። http://ethiopianobserver.wordpress.com/
 
    ኢትዮጵያ ጥፋተኛ ሆና ከተገኘች የአለፈው ሳምንቷ ድል ይሰረዝ እና ለቦትስዋና የ 3 ለ 0 አሸናፊነት እና ሙሉ ሶስት ነጥብ የሚሰጥ ሲሆን፣ የምድብ አንድ የደረጃ ሰንጠረዥን ኢትዮጵያ በ10 ነጥብ ስትመራ፣ ደቡብ አፍሪካ በስምንት ነጥብ ሁለተኛ፣ ቦትስዋና በሰባት ነጥብ ሶስተኛ፣ መሀከለኛው አፍሪካ ሪፐብሊክ በሶስት ነጥብ አራተኛ ደረጃን ይዘው የሚከተሉ ይሆናል። ስለዚህ ወደ ቀጣዩ ዙር የአለም ዋንጫ ማጣሪያ የሚያልፈውን የምድቡ አሸናፊ ለመለየት መሀከለኛው አፍሪካ ሪፐብሊክ ከ ኢትዮጵያ፤ ደቡብ አፍሪካ ከ ቦትስዋና የሚያደርጉት የምድቡ የመጨረሻ ጨዋታዎች ወሳኝ ይሆናሉ ማለት ነው።

ፊፋ በሶስት የአፍሪካ አገራት ላይ ማጣራት ሊያደርግ ነው


    አለም አቀፉ የእግር ኳስ ፌዴሬሽን (ፊፋ) በሶስት የአፍሪካ አገራት ላይ ማጣራት ሊያደርግ ነው።
ማጣራት የሚደረግባቸው አገራት ኢትዮጵያ ፣ ቶጎ እና ኢኳቶሪያል ጊኒ ሲሆኑ ፥ አገራቱ በ2014ቱ የብራዚል አለም ዋንጫ የማጣሪያ ጨዋታዎች የአለም አቀፉ የእግር ኳሰ ማህበር ህግን በጣሰ መልኩ ተጫዋቾችን አሰልፈዋል በሚል ነው ።
የኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድን ማጣራት የሚደረግበት ከቦትስዋና አቻው ጋር ጋቦሮኒ ላይ ባደረገው ጨዋታ ላይ ሁለት የማስጠንቀቂያ ካርድ ያየውን ምንያህል ተሾመን በመጠቀሙ ነው። በሚደረገው የማጣራት ሂደት ጉዳዩ እውነት ሆኖ ከተገኘ ዋልያዎቹ የ3 ነጥብ ቅጣት እንደሚጠብቃቸው ፊፋ በመግለጫው አስታውቋል።

     በተመሳሳይ የቶጎ ብሄራዊ ቡድን ከካሜሮን አቻው ፥ እንዲሁም የኢኳቶሪያል ጊኒ ቡድን ከ ኬፕቨርዴ አቻው ጋር ሲጫወቱ ተመሳሳይ ጥፋት በመፈጸማቸው ፊፋ በአገራቱ ላይ ምርመራውን ያደርጋል።
         ለአለም ዋንጫ ማጣሪያ ባደረግናቸው አምስት ጨዋታዎች ላይ ከኢትዮጵያ በኩል ቢጫ ካርድ የተመለከቱ ተጫዋችን ስም ዝርዘር ከፊፋ ድረገጽ በተገኘው መሰረት ከታች ቀርቧል።  እንደመረጃው ከሆነ ምንያህል ሁለት ቢጫ ካርድ ማየቱ እርግጥ ይመስላል። በነገራችን ላይ በረኛው ጀማል ጣሰው እና አይናለም ሃይሉ ትናንት ከደቡብ አፍሪካ ጋር ባደርግነው ጨዋታ ሁለተኛ ቢጫ ካርዳቸውን ያገኙ በመሆኑ በቀጣዩ ከሴንትራል አፍሪካ ጋር ባለን ወሳኝ ጨዋታ ላይ መሰለፍ አይችሉም።

1) June 3 2012 South Africa 1-1 ethiopia
~Sisay Bancha
~Abebaw Butako
~Minyahile Teshome BEYENE
~Addis Hintsa

2) June 10, 2012 Ethiopia 2-0 Central Africa
~Seyoum Tesfaye

3) March 24, 2013 Ethiopia 1-0 Botswana
~Jemal Tasew
~ Menyahile Teshome Beyene

4) June 8, Botswana 1-2 Ethiopia
~ Aynalem Hailu
~ Asrat Megersa Gobena

5) June 16, Ethiopia 2-1 South Africa
~Jemal Tasew
~Aynalem Hailu

ምንጭ     http://www.fifa.com      , DireSport

Friday, June 14, 2013

     የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ዛሬ ሰኔ 6/2005 የናይል ተፋሰስ የትብብር ማዕቀፍ ስምምነትን በሙሉ ድምፅ አፀደቀ፡፡
 ማዕቀፉ ኢትዮጵያ ያላትን የተፈጥሮ ሀብት ፍትሃዊ በሆነ መንገድ እንድትጠቀም ያስችላል ተብሏል፡፡ ከ10 አመት በላይ ድርድርና ውይይት የተካሄደበትና በ 6 የተፋሰስ ሀገራት ስመምነት የተፈረመበት የናይል ተፋሰስ የትብብር ማዕቀፍ በአለም አቀፍ ደረጃ ተቀባይነት ያለውን የድንበር ተሻጋሪ ወንዞች ህግ መሰረት ያደረገ ነው፡፡
    ማዕቀፉ እ.ኤ.አ በ1929 እና 1959 ዓ/ም የተካሄደውን የግብፅና ሱዳን በአባይ ውሃ ለብቻ የመጠቀም ስመምነትን የሚሽርም ነው፡፡ ፍትሃዊ የውሃ አጠቃቀምን በማረጋገጥ በጋራ መልማት የሚያስችለውን ይህን መርህ ኢትዮጵያ፣ ኬንያ፣ ሩዋንዳ፣ ታንዛንያ፣ ኡጋንዳና ቡሩንዲ ከፈረሙ ቆየተዋል፡፡
   ሀገራቱ የማዕቀፍ ስመምነቱን ከፈረሙ በኋላ ወደ ተግባር ለመግባት በሀገራቸው ፓርላማ ማፅደቅ ቀጣይ እርምጃ ነበር፡፡ይሁንና በግብፅ በተቀሰቀሰው አብዮት ምክንያት በፓርላማ የማፅደቅ ሂደቱ እንዲራዘም መደረጉን በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የመንግስት ተጠሪ ሚኒስትር አቶ ወንድሙ ገዛሀኝ ገልፀዋል፡፡
     የምክር ቤቱ አባላትም ኢትዮጵያ በተፈጥሮ ሀብቷ ተጠቅማ ድህነት ማስወገድ የሚያስችላት ስመምነት በመሆኑ ማዕቀፉ መፅደቅ እንደሚገባው አስተያየታቸውን  ሰጥተዋል፡፡ከምክር ቤቱ አባላት አዋጁ ለምን አሁ  መፅደቅ አስፈለገ የሚል ጥያቄም ተነስቷል፡፡
   የውሃ እና ኢነርጂ ሚኒስትሩ አቶ አለማየሁ ተገኑ ኢትዮጵያ ከወሰደቻቸው ትልልቅ ቅን እርምጃዎች አንዱ አዋጁን የማፅደቅያ ጊዜ ማራዘምዋ ነው ብለዋል፡፡ የምክር ቤቱ አባላትም በማዕቀፉ ላይ ሰፊ ውይይት ካደረጉ በኋላ በሙሉ ድምፅ አፅድቀውታል፡፡

በዳይመንድ ሊግ ውድድሮች መሀመድ አማን እና የኔው አላምረው አሸነፉ


     አዲስ አበባ ፣ ግንቦት 30 ፣ 2005   በተካሄዱ የዳይመንድ ሊግ ውድድሮች ኢትዮጵያውያኖቹ መሀመድ አማን እና የኔው አላምረው አሸነፉ። የአለም የቤት ውስጥ አትሌቲክስ አሸናፊው መሀመድ አማን በ800 ሜትር ፥ እንዲሁም የኔው አላምረው በ1500 ሜትር አሸናፊ ሆነዋል።
    መሃመድ አማን ርቀቱን በ1 ደቂቃ ከ43.61 ሰከንድ በሆነ ጊዜ በመግባት በርቀቱ የአመቱን ፈጣን ሰአት በማስመዝገብ ሲያሸንፍ ፥ ፈረንሳዊው ፒዬ-አምብሮስ እና ደቡብ አፍሪካዊው አንድሬ ኦሊቨር ሁለተኛ እና ሶስተኛ በመሆን አጠናቀዋል  ሰባት ውድድሮች በሚካሄዱበት የ800 ሜትር ውድድር ዳይመንድ ሊጉን ጉዳት ላይ ያለው የኦሎምፒክ እና የአለም ሻምፒዮኑ ኬኒያዊው ዴቪድ ሩዲሻ በስምንት ነጥብ ሲመራ ፣ መሀመድ አማን በስድስት ነጥብ ይከተላል።
         በወንዶች 5 ሺህ ሜትር ውድድር የተካፈለው ሌላው ኢትዮጵያዊ የኔው አላምረው ርቀቱን 12 ደቂቃ ከ54.95 ሰከንድ በሆነ ጊዜ በማጠናቀቅ የአመቱን ፈጣን ሰአት አስመዝግቦ አሸንፏል። የአሸናፊነት ግምቱን ያገኘው ሀጎስ ገብረህይወት በ12፡55.73 ሁለተኛ ሲሆን ፥ ኬኒያዊው አይሳያ ኮይች ሶስተኛ ደረጃን አግኝተው አጠናቀዋል። ዳይመንድ ሊጉን ሀጎስ ገብረህይወት በ10 ነጥብ ሲመራ ፣ የኔው አላምረው በአምስት ነጥብ ሁለተኛ ደረጃን ይዞ ይከተላል።
     በሴቶች 1500 ሜትር በጉጉት ሲጠበቅ የነበረው የኢትዮጵያዊቷ ገንዘቤ ዲባባ እና ዜግነቷን ከኢትዮጵያ ወደ ስዊድን የቀየረችው አበባ አረጋዊ ፉክክር በአበባ አረጋዊ የበላይነት ተጠናቋል። አበባ ርቀቱን 4፡00.23 በሆነ ጊዜ ስታጠናቅቅ ፥ ገንዘቤ በ4፡01.62 ሁለተኛ ፣ አሜሪካዊቷ ጄኒ ሲምሰን ሶስተኛ ሆነዋል። በርቀቱ ዳይመንድ ሊጉን አበባ አረጋዊ በ12 ነጥብ ስትመራ፣ ገንዘቤ ዲባባ በሶስት ነጥብ ሁለተኛ ደረጃን ይዛ ትከተላለች።
     በሴቶች 3 ሺህ ሜትር መሰናክል ሶፊያ አሰፋ ከወደቀችበት ተነስታ ርቀቱን 9፡21.24 በሆነ ጊዜ በሶስተኛነት ስታጠናቅቅ ፥ ውድድሩን ኬኒያዊቷ ሚልካ ቼሞስ የሀገሯን ልጅ ሊዲያ ቼፕኩሪን አስከትላ በመግባት በአሸናፊነት አጠናቃለች። በርቀቱ ዳይመንድ ሊጉን ሊዲያ ቼፕኩሪ በ10 ነጥብ ስትመራ፣ ሶፊያ አሰፋ እና ሚልካ ቼሞስ በእኩል አራት ነጥብ ይከተላሉ።ቀጣዩ የዳይመንድ ሊግ አትሌቲክስ ውድድር የፊታችን ሀሙስ በኖርዌይ ዋና ከተማ ኦስሎ ይካሄዳል።

የኢትዮጵያ አየር መንገድ የብቃት ደህንነት ተሸላሚ ሆነ


     በአፍሪካ ፈጣኑና እያደገ ያለው የኢትዮጵያ አየር መንገድ የ2013 የብቃት ደህንነት ለሶስተኛ ጊዜ ከቦምባርዴር ተሸላሚ መሆኑን አየር መንገዱ ገልጿል፡፡
    ሽልማቱ ለአየር መንገዱ የተሰጠው ለተጓዦች በአማካይ 99 በመቶ በሚያደርሰው መረጃ እና በ2012 ከተጓዦች በሰበሰበው የገቢ መጠን እንዲሁም በአጠቃላይ አየር መንገዱ በመካከለኛው ምስራቅና በአፍሪካ በሚያደርገው ቀልጣፋ የደንበኞች አገልግሎት ስራ ነው፡፡
በስነስርአቱ ላይ የአየር መንገዱ ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ ተወልደ ገብረማርያም እንዳሉት ፥ ሽልማቱ  በየቀኑ እያሻሻልን ላለነው የደንበኞች አገልግሎት ቀጣይነት እንዲኖረው የሚያደርግ ነው ብለዋል፡፡ አየር መንገዱ በአሁኑ ሰአት 13 Q-400 አውሮፕላኖችን የሚጠቀም ሲሆን ፥ ይህም ሰፊ አካባቢያዊ የበረራ መስመሮችን በመሸፈን በቱሪዝምና ንግድ እንቅስቃሴ ለሚጓዙ ደንበኞች በበቂ ሁኔታ ፍላጎታቸውን ለማማሟላት እንደሚያስችለው ነው የተገለጸው፡፡
    አየር መንገዱ በQ-400 አውሮፕላኖች በአገር ውስጥ ከሚያካሂደው አስራ ሰባት የበረራ መስመሮች በተጨማሪ በጅቡቲ፣ ሞምባሳ፣ ናይሮቢ፣ ኪሊማንጃሮ፣ ዳሬሰላም፣ ዛንዚባር፣ ኪጋሊ፣ ጁባ፣ ካርቱም፣ በርበራ እና ኢንቴቤ እየተጠቀመ ነው፡፡እ.ኤ.አ በ1946 የመጀመሪያውን አለም አቀፍ በረራ ወደ ካይሮ በማድረግ ስራውን የጀመረው የኢትዮጵያ አየር መንገድ በአራት አህጉሮች በ72 አለምአቀፍ የበረራ መዳረሻዎች ላይ እየሰራ ይገኛል፡፡

                                                    ምንጭ፦ የኢትዮጵያ አየር መንገድ

ግብፅ የትምክህት አስተያየቶችን ከመስጠት መቆጠብ አለባት - ዩዌሪ ሙሶቮኒ


 የኡጋንዳው ፕሬዝዳንት ዩዌሪ ሙሶቮኒ የግብፅ መንግስትና ሌሎች ቡድኖች የትምክህትና ምክንያታዊ ያልሆኑ አስተያየቶችን ከመሰንዘር አንዲቆጠቡ ማሳሰባቸውን ቺምፕ ሪፖርትስ ድረ ገፅ ዘግቧል፡፡
የኢትዮጵያ መንግስት የሚገነባውን የሃይል ማመንጫ ግድብ አስመልክተው የግብፅ መገናኛ ብዙሃን ዘገባዎችን አንብቤያለሁ፡፡ በዚህ ነገር የኢትዮጵያ መንግስት መደነቅ ነው የነበረበት፡፡  ይህ ሁሉም የአፍሪካ ሃገራት ሊተገብሩት የሚገባ ነው፡፡ የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ በሁለት አሃዝ ካደገባቸው ምክንያቶች ውስጥም አንዱ ይሄው ነው፡፡ ስለዚህ የግብፅ መንግስትም ሆነ በሃገሪቱ ያሉ ትምክህተኛ ቡድኖች የባለፉትን የግብፅ መሪዎች ስህተት መድገም የለባቸውም፡፡”
    አፍሪካ አሁን ግብፅ ጥቁር አፍሪካውያንን እንድትጎዳ የሚፈቅድ አህጉር አይደለም ብለዋል ፕሬዝዳንት ዩዌሪ ሙሶቮኒ ፡፡
“ማንም የአፍሪካ ሃገር ግብፅን መጉዳት አይፈልግም፡፡ ሆኖም ግብፅም ጥቁር አፍሪካውያንንና የአካባቢውን ሃገሮች እየበደለች መቀጠል የለባትም” ብለዋል፡፡ ግብፅ ያለፉት መሪዎቿን የተሳሳተ የፖሊሲ አቅጣጫ መከተል የለባትም ያሉት ሙሶቮኒ ለናይል ወንዝ ስጋት የሚሆነው የግድቦች ግንባታ ሳይሆን የሃይል አቅርቦት እጥረትና በአካባቢው ያለው ኋላቀርነት መሆኑን አብራርተዋል፡፡ 
 ትልቁ የናይል ወንዝ ስጋት ስር የሰደደው የልማት ኋላቀርነት ነው፡፡ ይህም በሃይል አቅርቦት እጥረትና በኢንዱስትሪ ያለመስፋፋት የሚገለፅ ነው፡፡ ሃይል ለማግኘትና ለዘልማዳዊ እርሻ ሲሉ አርሶ አደሮች ደኖችን ይመነጥራሉ፡፡ ይህ ደግሞ የአካባቢውን የተፈጥሮ ሚዛን ያዛባል፡፡”
ዩዌሪ ሙሶቮኒ ይህን ሃሳባቸውን ለቀደሙት የግብፅ መሪዎችም ሆነ ለአሁኖቹ እንደመከሩ ተናግረዋል፡፡ አሁንም ከግብፅ በኩል የሚሰነዘሩ የትምክህት አስተያየቶች እንዲቆሙና በስሜት ላይ ሳይሆን በምክንያት ላይ የተመሰረተ ውይይት በሁለቱ ሃገራት መካከል እንዲካሄድ መክረዋል፡፡
                                                                 ምንጭ፤ ቺምፕሪፖርትስ

Saturday, June 8, 2013

የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ 166 የህክምና ዶክተሮችን አስመረቀ

     ከተመረቁት መካከል 36ቱ ሴቶች ሲሆኑ ይህም ሃገሪቱ በጤናው ዘርፍ የሴቶችን ተሳትፎና የምዕተ አመቱን የልማት ግብ ለማሳካት የምታደርገውን እንቅስቃሴ የሚያጠናክር መሆኑ በምረቃው ስነ ስርዓት ላይ ተገልጧል፡፡በስነ ስርዓቱ ላይ የፌዴሬሽን ምክር ቤት አፈ ጉባዔና የአዲስ አበባ ዩንቨርስቲ ቦርድ ሰብሳቢ አቶ ካሳ ተክለብርሃን እንዳሉት ኢትዮጵያ የጤናውን ዘርፍ ልማት ለማሳደግ በጀመረችው ጉዞ ከፍተኛ ቁጥር ያላቸውን የህክምና ባለሙያዎችን ለማፍራት እየሰራች ነው፡፡
 
    “ተመራቂዎች በጤናው ዘርፍ የተገኙ ድሎችን ቀጣይነት ለመድገም በስነ ምግባር ታንፃችሁ ሃገሪቱንና ህዝቦቿን ማገልገል ይኖርባችኋል” ብለዋል አቶ ካሳ ተክለብርሃን ፡፡ ጤናው የተጠበቀ አምራች ዜጋ ለማፍራትና መንግስት ለከፍተኛ ትምህርት በሰጠው ልዩ ትኩረት ኮሌጁ ከአመት ወደ አመት የቅበላ አቀቅሙን እያሳደገ መምጣቱን የገለፁት ደግሞ የዩንቨርስቲው ፕሬዝዳንት ዶክተር አድማሱ ፀጋዬ ናቸው፡፡
 
      ተመራቂ ዶክተሮች ግንባር ቀደም የጤና ሰራዊት ሆነው ወደተለያዩ የሀገሪቱ ክልሎች በመሄድ የጤናው ሽፋን የማሳደግ ሃላፊነታቸውን እንዲወጡ ፕሬዝዳንቱ አሳስበዋል፡፡
ተመራቂዎችም የሙያውን ስነ ምግባር ጠብቀው ሃላፊነታቸውን ለመወጣትና ህዝቡን በላቀ ተነሳሽነት ለማገልገል መዘጋጀታቸውን ገልፀዋል፡፡

     ለ2006 154 ነጥብ 9 ቢሊዮን ብር ረቂቅ በጀት ተዘጋጀ

    የሚኒስትሮች ምክር ቤት ዛሬ ግንቦት 30/2005  ባካሄደው 49ኛው መደበኛ ስብሰባ የ2006 በጀት አመት የፌዴራል መንግስት ረቂቅ በጀት ላይ ተወያይቶ 154.9 ቢሊዮን ብር እንዲሆን ውሳኔ አሳለፈ፡፡
   በዚህ መሰረት ለ2006 በጀት አመት በፌዴራል መንግስት ለሚከናወኑ ስራዎችና አገልግሎቶች የሚያስፈልገውን በጀት አጽድቆ በበጀት አመቱ መጀመሪያ ወቅት ስራ ላይ ማዋል አስፈላጊ በመሆኑ እና የፌዴራሽን ም/ቤት በወሰነው ቀመር መሰረት የፌዴራሉ  መንግት ለክልሎች የሚሰጠውን የድጋፍ በጀት መጠን መወሰን ስለሚኖርበት ከሐምሌ 1 ቀን 2005 ዓ.ም ጀምሮ እስከ ሰኔ 30 ቀን 2006 ዓ.ም በሚፈጸመው በአንድ የበጀት አመት ጊዜ ውስጥ የፌዴራል መንግስት በጀት 154,903,290,899/ አንድ መቶ ሃምሳ አራት ቢሊዮን ዘጠኝ መቶ ሶስት ሚሊዮን ሁለት መቶ ዘጠና ሺህ ስምንት መቶ ዘጠና ዘጠኝ ብር/ እንዲሆን ወስኗል፡፡
ከዚህ ውስጥ፡-
·         ለመደበኛ ወጪዎች--------------------ብር 32,530,000
 ·        ለካፒታል ወጪዎች ------------------- ብር 64,321,732,351
 ·         ለክልሎች የሚሰጥ ድጋፍ --------------- ብር 43,051,558,548
 ·         የምዕተ ዓመቱን ልማት ግቦች ማስፈጸሚያ ድጋፍ-- ብር 15,000,000,000 እንዲሆን ተመድቧል፡፡
 የሚኒስትሮች ምክር ቤት  በቀረበው ረቂቅ በጀት ላይ በስፋት ከተወያየ በኋላ ይጸድቅ ዘንድ ለህዝብ ተወካዮች ም/ቤት አስተላልፏል፡፡

Tuesday, June 4, 2013

                             Meles Zenawi


  •  Nationality Ethiopian
  • Date of Birth 8 May 1955
  •  Occupation Politician
  • Education Open University, Erasmus University Rotterdam
  • Meles Zenawi Children Senay Meles, Semhal Meles, Marda Meles 
          He joined the Tigrayan People’s Liberation Front (TPLF) as a member in 1975. Eventually, he was elected as the chairperson of TPLF and EPRDF. Lead by him and other leaders, TPLF was able to assume power in the country in 1991 as the civil war came to an end. Upon becoming the Prime Minister, he introduced a multi-party political system and allowed private press in the country. He agreed to work with the United States against groups and organizations such as Al Qaeda operating out of the country.

        He was awarded the Rwanda’ National Liberation Medal and also the “World Peace Prize” for his contributions to global peace. Zenawi also received the “Yara” prize for carrying out a green revolution in the country. Some other awards he had received included the Africa Political Leadership Award in 2008, and the Good Governance award.

        He married Azev Mesfin, who is currently a member of the Ethiopian Parliament. Meles Zenawi died at the age of 57 years on the 20th of August, 2012. He died from an infection after having an operation due to a brain tumor.

       Meles Zenawi Net Worth

 Net Worth: Stats $3 Billion

  • Source of Wealth politics
  • Meles Zenawi Age 58years old
  • Meles Zenawi Birth Place Adwa, Ethiopia
  • Meles Zenawi Marital Status Married (Azeb Mesfin)

 

      Meles Zenawi net worth: Meles Zenawi Asres was the former Prime Minister of Ethiopia who presided over the country from 1995 to his death in 2012. He was also the President of Ethiopia from 1991 to 1995. He was one of the most recent literate and forward thinking leaders of Africa. Zenawi had an MBA from the United Kingdom, and a Masters of science in economics from Netherlands. His net worth currently stands at $3 Billion.

Saturday, June 1, 2013

Bekele wins 10,000 meters at Pre Classic


     Distance runner Kenenisa Bekele, from Ethiopa, crosses the finish line to win the 10,000-meter race during the Prefontaine Classic track and field meet in Eugene, Ore., Friday, May 31, 2013. Bekele won with a time of 27:12.08. (AP Photo/Don Ryan)
         EUGENE, Ore. (AP) — World record-holder Kenenisa Bekele took the lead heading into the final lap and sprinted to the finish to win the 10,000 meters at the Prefontaine Classic on Friday night. Bekele finished in 27 minutes, 12.08 seconds, ahead of fellow Ethiopians Imane Merga and Abera Kuma.
     London Olympic gold medalist Mo Farah withdrew from the race a day earlier because of a stomach bug, instead choosing to run Saturday in the 5,000 in the elite Diamond League meet at Hayward Field.Bekele set the meet record in the 10,000 at the Prefontaine back in 2008, when he ran it in 26:25.97. He went on to win gold medals in the 10,000 and 5,000 in the Beijing Olympics that year.
"It's a very special place," Bekele said. "In this stadium I had the time 26:25 so I'm happy to run here again. It is a good atmosphere, many people supporting us."