Friday, March 20, 2020

አዲስ መጽሐፍ በቅርብ ቀን!!


በምድራችን  ላይ  ከምናውቀው  ሀቅ  የራቁና  ያፈነገጡ፣  ከፊዝክስና ሥነ- ሕይወታዊ  የተፈጥሮ  ህጎችም  የወጡ  እውነቶች  በገሀዱ  ዓለም  መኖራቸውን  ያውቀሉ ?   “ እንዴት? ”  አሰኝተው  አዕምሮን  በጥያቄ  የሚፈትሩ!

የሳይንሱን  ዓለም  በጥያቄ  የወጠሩና  በተደምሞ  ዝም  ያሰኙ  ክስተታዊ  እውነቶችንስ  ምን  ማለት  ይቻላል?

ለመሆኑ  የሰው  ልጅ  አውቄዋለሁ  ብሎ  የተረከውን  ጥንታዊ  ታሪኩንና  ጂኦግራፊን  እንደገና  ለመጻፍ  የሚያስገድደው  ማስተካከያ  ይመጣ  ይሆን?

እንዲህ  ማፈትለኩ  ላይቀር  ማስረጃና መረጃን በማጥፋት አስገራሚ ግኝቶችን ለመደበቅ፣ ለማጥፈትና  እንደሌሉ ለማድረግ  ኃያላኑ የሚሰሩት  ለምን  ይሆን?

በየእለቱ  የማይለይዎትንና  ያለምንም  ማመንታት  “በደንብ  አውቀዋለሁ!”  የሚሉትን  ነገር  “ የለም  አያውቁትም! ”  ቢባሉ  ምን  ይሰማዎታል?  እንደማያውቁት  ቢረዱስ  ምን  ይላሉ? 

Ø   “ፍ ን ግ ጥ”  አንብበው  ይደመማሉ!  በቅርብ  ቀን  ይጠብቁን!   
____________________________
በብዙ  እንቆቅልሽ  ድንቆች  የተሞላች
ቅርብ  መሳይ  ጠሊቅ  በእጅጉ  የራቀች
ምድራችን  ጥያቄ  ረቂቅ  ምስጢር  ነች
የፈጣሪ  ቅኔ  ገና  ያልተፈታች!

No comments:

Post a Comment