Sunday, February 23, 2014

የኢትዮጵያ አየር መንገድ ወደ ለንደን በየቀኑ በረራ ሊጀምር ነው


 
    በአፍሪካ በፈጣን እድገት ላይ የሚገኘው እና ትርፋማ የሆነው የኢትዮጵያ አየር መንገድ ወደ ለንደን በየቀኑ መብረር መጀመሩን አስታወቀ፡፡ የአየር መንገዱ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ ተወልደ ገብረማርያም እንደገለጹት እንደ አውሮጳውያን አቆጣጠር ከ1973 ጀምሮ  እስካሁን ድረስ ጥሩ አገልግሎት እየሰጠ ነው፡፡    
        
    የአየር መንገዱ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ ተወልደ ገብረማርያም በሰጡት አስተያየት ‘‘በየቀኑ ወደለንደን የበረራ አገልግሎት መስጠት በመጀመራችን ከፍተኛ ደስታ ተሰምቶናል ደንበኞቻችንም ምቾት ያለው እና አስተማማኝ በረራዎቸን በዘመናዊ የቦይንገ 787 አውሮፕላኖች ማድረግ ይችላሉ፤ አውሮፕላኖቹም የድምጽ ብክለትን የሚቀንሱ ፣ሰፋፊ መስኮት ያላቸው እና ከፍተኛ ምቾት የሚሰጡ ናቸው፡፡’’ ብለዋል፡፡ አየር መንገዱ ወደ ለንደን በየቀኑ የሚያደርገውን በረራ የሚጀምረው እንደ አውሮጳውያን አቆጣጠር ሐምሌ 8 ቀን 2014 ነው።

     አቶ ተወልደ ገብረማሪያም ለንግድ ስራም ሆነ ለመዝናናት ወደ ለንደንና ወደ 48 የአፍሪካ መዳረሻዎች ለሚመላለሱ ደንበኞች በየቀኑ አጫጭር የበረራ አገልግሎት እንደሚሰጥም አስታውቀዋል። አየር መንገዱ ዘመናዊ በሆኑት ቦይንግ 777 እና ቦይንግ 787 ድሪምላይነር አውሮፕላኖችን በመጠቀም በቀን 200 በረራዎችን የሚያደርግ ሲሆን  በአምስት አህጉራት ላይ 79 መዳረሻዎች እንዳሉት ተጠቅሷል::

No comments:

Post a Comment