Tuesday, February 4, 2014

ኢትዮጵያኖቹ በዓለም የሩጫ አደባባይ ባለ ድል ሆነዋል

    ባለፈው ቅዳሜና እሁድ በተለያዩ ሀገሮች በተካሄዱ የሩጫ ውድድሮች ኢትዮጵያኖቹ መሀመድ አማን፣ ህይወት አያሌውና ገንዝቤ ዲባባ ውድድራቸውን በቀዳሚነት አጠናቀዋል፡፡
     ጥር 25/2006 በሞስኮ የ6 መቶ ሜትር የቤት ውስጥ ውድድር የተሳተፈው የ8 መቶ ሜትር ሻምፒዮኑ መሀመድ አማን በስፍራው ለአዲስክብረወሰን ቢጠበቅም ከልክ ያለፈው የሞስኮ ቅዝቃዜ መሀመድን ለትንሽ ከክብረ ወሰኑ ገትቶታል፡፡መሀመድ አማን ውድድሩን በቀዳሚነት ቢያጠናቅቅም አዲስ የአለም ክብረወሰን ለማስመዝገብ በ19 ማይክሮ ሰከንድ ብቻ ዘግይቶ እንደገባ ተዘግቧል። 
   በቤት ውስጥ ውድድር ሁለት ጊዜ ክብር ወሰን የሰበረችው የጥሩነሽ ዲባባ ታናሽ እህት ገንዘቤ ዲባባ ፣እንድ ጥሩነሽ ሁሉ የራሷን ታሪክ በዓለም የሩጫ መድረክ  መስራት ቀጥላለች፡፡ ገንዘቤ ባለፈው ቅዳሜ በጀርመን የተካሄደውን የ1ሺህ 5 መቶ ሜትር የቤት ውስጥ ውድድር 3፡55፡17 በሆነ ሰዓት በመግባት የርቀቱን ክብር ወሰን በእጇ አስገብታለች፡፡
  "በማሸነፌ በጣም ደስተኛ ነኝ እርቀቱን ከዚህ ያነሰ ሰዓት በመግባት ክብር ወሰኑን ለመያዝ ጠንካራ ስራ እሰራለሁ ብላለች "ገንዘቤ ከውድድሩ በኋላ ለአለም አቀፉ አትሌቲክስ ፌደሬሽን በሰጠችው ቃለ ምልልስ፡፡
     ህይወት አያሌው በበኩሏ እሁድ በፈረንሳይ በተካሄደው አገር አቋራጭ ውድድር በድንቅ ብቃት ቀዳሚ ሆና ገብታለች፡፡ ህይወት በዓመቱ በጎዳና ላይ ያደረገቻቸውን ውድድሮች በሙሉ ማሸነፍ የቻለች ሲሆን የእሁዱ አሸናፊነት 6ኛዋ ነው፡፡

No comments:

Post a Comment