በተቀናጀ
የወንዞች ተፋሰስ ልማት አስተዳደር የድህረ ምረቃ ትምህርቱ ዓላማ የተጀመረውን የእድገትና ትራንስፎርሜሽን እቅድ
መሰረት በማድረግ የውሃ አጠቃቀም፣ የመሬት ልማትና የተፈጥሮ ሃብት እንክብካቤን በማሻሻል የተቀናጀ የልማት አቅጣጫ
በመከተል ምርትን በእጥፍ ለማሳደግ እንደሆነ ገልጸዋል።

ትምህርቱ ምርትን በማሳደግ የህዝቡን ኑሮ በማሻሻል አከባቢ ሳይጎዳ ከአቅም በላይ የህዝብ መጨናነቅ ሳይፈጠር ያለውን ሃብት በበቂ ሁኔታ ለህብረተሰቡ ለማዳረስ የሚረዳ መሆኑንም ዶክተር እያሱ አስታውቀዋል።
የትምህርት
ዘርፉ በምስራቅ አፍሪካ የሚታየውን የውሃ እጥረት፣ የመሬት ለምነት መቀነስና የህዝብ ቁጥር መጨመር የሚያስከትለውን
የሃብት አለመመጣጠን በማቃለል በሃገሮች መካከል መልካም ጉርብትናና ወንድማማችነትን ለማሻሻል እንደሚያግዝ ዶክተር
እያሱ ገልጸዋል ሲል ኢዜአ ዘግቧል።
No comments:
Post a Comment