Thursday, March 19, 2020

ደራሲ እና መምህር ሲሳይ ንጉሱ…..

1951 . እዚሁ አዲስ አበባ ውስጥ ደጃች ውቤ /ውቤ በረሃ/ ነው የተወለደው፡፡ አንደኛ ደረጃ ትምህርቱን በባልቻ አባነፍሶ ሁለተኛ ደረጃን ደግሞ በአዲስ ከተማ አጠቃላይ /ቤት ተከታትሏል፡፡ከዚያም 1974 . አስመራ ዩኒቨርስቲ ገብቶ በስነ ፅሁፍ እና ቋንቋ 1977 . የመጀመሪያ ዲግሪውን አግኝቷል፡፡ 11 ክፍል እያለጉዞውየተሰኘ ኖቬላን የመጀመሪያ ስራው አድርጎ አሳትሟል፡፡ይህንን ጨምሮ 6 ያህል መፅሃፍትን እስካሁን ለአንባቢያን አድርሷል፡፡


ሰመመንየተሰኘው የረጅም ልብ ወለድ ድርሰቱ ከፍተኛ ተነባቢነትን በአጭር ጊዜ ውስጥ ያገኘለት ስራው ሲሆን በወቅቱም 60 ያህል ቅጂዎች ተሸጠውለታል፡፡በ1978 . የታተመው እና 378 ገፆች ያሉትሰመመንበዩኒቨርስቲ ህይወት ዙሪያ እና በፍቅር ታሪክ ላይ ያተኩራል፡፡ መፅሃፉ የተፃፈው ደራሲ ሲሳይ ንጉሱ በአስመራ ዩኒቨርሰቲ 3 አመት ተማሪ እያለ ነበር ፡፡
የደራሲው ሥራዎች፡-
1. ጉዞው ( ኖቬላ ) – 1975 .
2.
ሰመመን ( ልብ ወለድ ) – 1977/8 .
3.
ግርዶሽ ( ልብ ወለድ ) – 1981 .
4.
ትንሳኤ ( ›› ›› ) – 1983 .
5.
የቅናት ዛር ( ›› ›› ) – 1988 .
6.
ረቂቅ አሻራ ( ›› ›› ) – 1995 .
 “ሰመመንየተሰኘው ድርሰቱን በኩራዝ አሳታሚ ድርጅት ሲያሳትም፤ ግርዶሽ፣ ትንሳኤ፣ የቅናት ዛር እና ረቂቅ አሻራን በአርቲስቲክ እና ሜጋ ማተሚያ ድርጅቶች በግሉ ነው ያሳተማቸው፡፡ 1983 . አርቲስቲክ ማተሚያ ቤት የታተመውንትንሳኤመፅሃፍ መታሰቢያነቱን በፋሽስቶችቀይ ሽብርለወደቅው /ለሞተው/ አጎቱ ለታምሩ ተክሉ አድርጓል፡፡ በዚሁ ማተሚያ ቤት 1995 . የታተመውረቂቅ አሻራደግሞ ማስታወሻነቱን ለባለቤቱ ብስራት አሰፋ እና ለልጁ ትንሳኤ ሲሳይ ይሁንልኝ በማለት ነው ለአባቢያን ያበረከተው፡፡
አስመራ ዩኒቨርሰቲ እያለ የስነ ፅሁፍ እና የቲያትር ክበብ መስርቶ ይንቀሳቀስ ነበር፡፡ ’’ብዕር አምባ’’ በሚል ስያሜ፡፡ 4 አመት የዩኒቨርሰቲ ተማሪ እያለም ‘’ስዊት ዲስ ኦርደር’’ የሚል ቲያትር ደርሶ ለእይታ አብቅቷል፡፡ ቲያትሩ በአሉላ አባ ነጋ አዳራሽ የታየ ሲሆን በወቅቱም በተመልካች ዘንድ ተወዳጅ ነበር፡፡ በዚህ ቲያትር ላይ ሲሳይም በተዋናይነት ተሳትፏል፡፡

አስመራ ዩኒቨርሰቲ 2 አመት ካስተማረ በኋላ ሙሉ ጊዜውን ለስነ ፅሁፍ በማድረግ ግርዶሽ የተሰኘውን ድርሰቱን አሳትሟል፡፡ ይህ መፅሃፍም ሰመመንቀጥሎ ከፍተኛ ሽያጭ ነበረው ፡፡ በአጭር ጊዜ ውስጥም 40 ቅጃዎች ተሸጦለታል፡፡ ደራሲና መምህር ሲሳይ ንጉሱ 10 ዓመታት ያህል በኢትዮጵያ ደራሲያን ማህበር በዋና ፀሀፊነት አገልግሏል፡፡ ካለፉት የተወሰኑ አመታት ጀምሮ ደግሞ ውጪ ከሚገኙ ወዳጆቹ እና ጓደኞቹ ጋር በመሆን አንድነት ኢነተርናሽናል /ቤትን ከፍተው በአመራርነት እየሰራ ይገኛል፡፡ ደራሲ ሲሳይ ንጉሱ 1991 . ከኢትዮጵያ ስነ ጥበባት እና መገናኛ ብዙሃን ሽልማት ድርጅት በስነ ፅሁፍ ዘርፍ ተሸላሚ ነበር፡፡በወቅቱም 20 ብር፣ የክብር ዲፕሎማ እና የወርቅ ሜዳሊያ ተበርክቶለታል፡፡ በያዝነው አመትም በትምህርት አስተዳደር እና አመራር የማስተርስ ዲግሪውን አግኝቷል፡፡ ስለ ደራሲና መምህር ሲሳይ ንጉሱ እኔ ከአንደበቱ የሰማሁትን ይህን አካፈልኳችሁ ቀሪውን ደግሞ እናንተ ጨምሩበት……….   !!!!

No comments:

Post a Comment