Thursday, September 25, 2014

የዓለም አቀፉ አማራጭ የኖቤል ሽልማት ተሸላሚ - ዶ/ር ተወልደብርሃን ገብረእግዚአብሔር

  
   / ተወልደብርሃን ገብረእግዚአብሔር በአካባቢ ጥበቃ ዘርፍ ላደረጉት ምርምርና በጉዳዩ ዙሪያ ከፍተኛ ግንዛቤ እንዲፈጠር ላደረጉት ጥረት በፈረንጆቹ 2002 ዓመት - ዓለም አቀፉን አማራጭ የኖቤል ሽልማት (Alternative Nobel Prize) በስቶኮሆልም ስዊዲን ተሸልመዋል፡፡
  
  / ተወልደብርሃን በፈረንጆቹ 2006 ዓመትም የተባበሩት መንግሥታት በአካባቢ ጥበቃ ዙሪያ ከፍተኛ አስተዋጽኦ ላደረጉ ሰዎች የሚሸልመውን የምድራችን ጀግና - Champions of the Earth ሽልማት አግኝተዋል፡፡ ይህን ሽልማት ያገኙት ሰባት ብቻ ናቸው፡፡ የዚህ ሽልማት ተቋዳሽ ከሆኑት መካከል የቀድሞ የሩሲያ ፕሬዚዳንት ሚኻኤል ጎርቫቾቭ አንዱ ነበሩ፡፡
 
  / ተወልደብርሃን ገብረእግዚአብሄር የታዋቂው ደራሲና ጋዜጠኛ ስብሐት ገብረእግዚአብሔር ታናሽ ወንድም ናቸው፡፡ አፍሪካውያን / ተወልደብርሃንን - የአፍሪካ ድምጽ - The Voice of Africa እያሉ ይጠራቸዋል ያንቆለጳጵሳቸዋል፡፡


No comments:

Post a Comment