Saturday, March 28, 2015

ኢትዮጵያ በቻይና ጉያንግ የአለም አገር አቋራጭ ውድድር በበላይነት አጠናቀቀች ።


   41ኛውን የአለም አገር አቋራጭ ውድድር ኢትዮጵያ በአጠቃላይ 5 የወርቅ 3 የብርና 3 የነሃስ ሜዳሊያ በማግኘት ነው ቀዳሚ የሆነችው። ኢትዮጵያ በስድስት ኪሎ ሜትር ወጣት ሴቶች እና በስምንት ኪሎ ሜትር ወጣት ወንዶች የወርቅ ሜዳሊያዎችን ስታገኝ፥ በስምንት ኪሎ ሜትር አዋቂ ሴቶች ደግሞ የብርና የነሃስ ሜዳሊያ አግኝታለች።

 በሴቶች ስድስት ኪሎ ሜትር ወጣት ሴቶች ለተሰንበት ግደይ፣ ደራ ዲዳ እና እታገኝ ወልዱን አስከትላ በመግባቷ ኢትዮጵያ በቡድንም የወርቅ ሜዳሊያ እንድታገኝ አድርገዋል። በ8 ኪሎ ሜትር ወንዶችም ያሲን ሀጂ በአንደኝነት በማጠናቀቅ የወርቅ ሜዳለያ አግኝቷል።

  በ8 ኪሎ ሜትር አዋቂ ሴቶች በተካሄደው ውድድር ሰንበሬ ተፈሪ እና ነፃነት ጉደታ የብር እና የወርቅ ሜዳልያ ለአገራቸው አስገኝተዋል።

   በ12 ኪሎ ሜትር አዋቂ ወንዶች ውድድር ሙክታር እንድሪስ 3ኛ ሆኖ በማጠናቀቅ የነሃስ ሜዳልያ ለኢትዮጰያ ሲያስገኝ፣ ሀጎስ ገብረህይወት እና ታምራት ቶላ 4ኛ እና 5ኛ ሆነው አጠናቀዋል።  በዚህም በቡድን ባመጡት ውጤት 5ኛ ወርቅ ኢትዮጵያ ማግኘት ችላለች። 
                                                ምንጭ ፡- ኤፍ.ቢ.ሲ 

No comments:

Post a Comment