ኢትዮጵያና ኡጋንዳ በሆቴል ዘርፍ ከፍተኛ ኢንቨስትመንት እያስመዘገቡ ከሚገኙ ከሰሀራ በታች ካሉ አምስት የአፍሪካ ሀገሮች ተርታ ተሰልፈዋል፡፡ ደብሊው ሆስፒታሊቲ የተሰኘ ድርጅት ደረጃቸውን ከጠበቁ አለማቀፍና አህጉር አቀፍ እንዲሁም ትናንሽ ሆቴሎች ላይ የዳሰሳ ጥናት ካካሄደ በኋላ ነው መረጃውን ይፋ ያደረገው፡፡

በያዝነው
ዓመት በዘርፉ በሚፈጠር የስራ እድልን ማዕከል በማድረግ በወጣው ደረጃ ፣ናይጄሪያ በሆቴል ኢንቨስትመንት ቀዳሚ
የኢንቨስተሮች መዳረሻ እንደምትሆን የተቀመጠ ሲሆን 53 ሺህ የስራ እድል በዘርፉ እንደሚፈጠር ተመላክቷል፡፡ በኢትዮጵያም 8 ሺህ 8 መቶ የስራ እድል እንደሚፈጠር ተጠቁሟል፡፡ ምንጭ፦ኒው ቪዥን
No comments:
Post a Comment