Saturday, September 24, 2022

ከ1ኛ ክፍል እስከ ዶክተርነት ሕልማቸውን ያሳኩ 16 አብሮ አደጎች….


የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ የጤና ሳይንስ ኮሌጅ ዘንድሮ በመጀመሪያ ዲግሪ ከሚያስመርቃቸው 250 ከሚበልጡ የህክምና ተማሪዎች ውስጥ 16 ከልጅነት ጀምሮ የሚተዋወቁ ወላይታ ሊቃ ከተባለ ትምህርት ቤት አብረው የመጡ ወጣቶች ናቸው፡፡

አብሮ አደገቹ ከለጋ እድሜያቸው አንስቶ ሀኪም የመሆን ልዩ ፍላጎት የነበራቸው ሲሆን ህልማቸውን እውን ለማድረግም አብሮ በማጥናት እና በመደጋገፍ ሲተጉ መቆየታቸውን ይገልጻሉ፡፡ የዚህ ትልማቸው መነሻ የጀመረውም ወላይታ ሊቃ በወላይታ ልማት ማህበር (ወልማ) በተቋቋመው ትምህርት ቤት ነው።

 16 ጓደኛማቾች መሃል አብዛኛዎቹ ከአንደኛ ክፍል ጀምሮ አብረው የተጓዙና ጠቂቶቹ ደግሞ ከአምሰተኛ ክፍል ተቀላቅለዋቸው እስከ 12 ክፍል ድረስ በትምህረፍት ቤቱ ቆይታ አድርገዋል። የወላይታ ሊቃ ትምህርት ቤት መምህራን ዛሬ ለደረስንበት ደረጃ የማይተካ ሚና ነበራቸው የሚሉት ሀኪሞቹ ግንኙነታቸው የተማሪ እና የአስተማሪ አይነት ሳይሆን የወላጅ እና የልጅ እንደነበረ ያስታውሳሉ። 

 


ወላይታ ሊቃ ትምህርት ቤት አቅም በፈቀደ በእውቀት የዳበረ እና ራዕይ ያለው የተማረ የሰው ኃይል ለማፍራት ከሚያደርገው ጥረት ባሻገር፣ ተማሪዎችን በመልካም ስብዕና ለማነፅ የነበረው ቁርጠኝነት ለዛሬ የተሟላ ስብዕናቸው መሠረት እንደነበርም አውስተዋል። 

 አብሮ አደገቹ ሐኪሞች ዩኒቨርስቲ ከገቡም በኋላ ግንኙነታቸው ይበልጥ ተጠናክሮ ያለፉትን 7 ዓመታት በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ የጥቁር አንበሳ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል በብርቱ ወንድማማችነት ያሳለፉ ሲሆን፣ በግቢ ቆይታቸውም የሕክምና ትምህርት የሚጠይቀውን ትዕግሥት እና ትጋት ማዳበራቸውን ለኢዜአ ተናግረዋል።

No comments:

Post a Comment