Friday, June 12, 2015

ገንዘቤ ዲባባ በኦስሎ ዳይመንድ ሊግ አሸነፈች


  በኦስሎ በተካሄደ የ5ሺህ ሜትር ውድድር ገንዘቤ ዲባባ የእህቷን ክብረወሰን ባታሻሽልም አሸናፊ መሆን ችላለች። ገንዘቤ በውድድሩ ላይ ጥሩነሽ ዲባባ ከያዘችው የክብረወሰን ሰዓት በ10 ሰከንድ ዘግይታ በመግባቷ ነው ክብረወሰኑን ማሻሻል ያልቻለቸው። ጥሩነሽ ዲባባ ይህን የ5 ሺህ ሜትር ርቀት በጎርጎሮሳውያኑ 2008 ላይ 14:11.15 በሆነ ሰአት በመግባት የክብረ ወሰኑ ባለቤት ነች።


    ገንዘቤ ርቀቱን 14:21.29 በሆነ ሰዓት የሀግሯን ልጅ ሰንበሬ ተፈሪ እና ኬኒያዊቷን ቪዮላ ጂላጋት ኪቢዎትን በማስከትል አጠናቃለች። ገንዘቤ ከውድድሩ በኃላ ክብረ ወሰን ለማሻሻል አስባ ብትሮጥም አሯሯጮች በምትፈለግው ፍጥነት ስላልሄዱላት ክብረ ወሰኑን የማሻሻሽ እቅዷ እንዳልተሳካ ተናግራለች።

No comments:

Post a Comment