Friday, December 26, 2014

የሀረር ጀጎል - ግንብ


   የሀረር ህዝብ ታሪክ ባህል እና ማንነት ከሀረር ከተማ ጋር በእጅጉ የተቆራኘ ነው፡፡ ሀረሪዎች በረዥም ዘመን የስልጣኔ ታሪካቸው ያፈሯቸው ተንቀሳቃሽ እና የማይንቀሳቀሱ እንዲሁም የሚዳሰሱ እና የማይዳሰሱ በርካታ ቁሳዊ እና መንፈሳዊ ቅርሶች ባለቤት ናቸው፡፡ ከእነዚህ ቅርሶች መካከልም የከተማዋ ልዩ መለያ ምልክት ከመሆንም አልፎ .. 2006 በአለም ቅርስነት የተመዘገበው የጀጎል ግንብ በቀዳሚነት ይጠቀሳል፡፡ በግንቡ ውስጥም 82 በላይ መስኪዶች እና በርከት ያሉ የሀረሪ ባህላዊ ቤቶች ይገኛሉ፡፡
  

  ሀረር ከፍተኛ የስልጣኔ እድገት ደረጃ ላይ በደረሰችበት በ16ኛው ክፍለ ዘመንም በምስራቅ አፍሪካ የእስልምና ሀይማኖት ትምህርት እና የንግድ ማዕከል ሆናም አገልግላለች፡፡ ይህም የበርካታ ታሪካዊ እና ባህላዊ ቅርሶች ባለቤት እንድትሆን አድርጓታል፡፡ የጀጎል ግንብ የሀረሪ ህዝብ የኪነ ህንፃ ችሎታውን የሚያስመሰክር የታሪክ እና የጥበብ መዘክር ነው፡፡ ይህ ግንብ በ16ኛው ክፍለ ዘመን አጋማሽ በአሚር ኑር አማካኝነት እንደተገነባም ይነገራል፡፡
     የጀጎል ግንብ ከፍታ -------- ከ 4.5 እስከ 5 ሜትር
       ››     ›› ውፍረት ------- ከ40 እስከ 50 ኢንች
       ››     ›› ስፋት --------- 48
       ››     ›› በሮች ------ ሰባት ሲሆኑ አምስቱ ጥንታዊ በሮች ሲሆኑ ሁለቱ ደግሞ እ.ኤ.አ ከ1987 በኋላ የተከፈቱ እንደሆኑ መረጃዎች ይጠቁማሉ፡፡

  ሀረር ከቅርስነት ባሻገር እ.ኤ.አ በ2003/4 በሰላም ፣ በመቻቻል ፣ በመፈቃቀር እና በልማት ከተማነት አለም አቀፍ ሽልማት እና እውቅናን አግኝታለች፡፡ ይህም የተለያየ እምነት ፣ ባህል እና ቋንቋ ያላቸው ህዝቦች ለዘመናት በሰላም እና በፍቅር የኖሩባት እና ዛሬም የሚኖሩባት ከተማ በመሆኗ የተቀዳጀችው ክብር እና እውቅና ነው፡፡

No comments:

Post a Comment