Friday, February 21, 2014

ሱፐር ሞዴል ገሊላ በቀለ "ኔስፕሪሶ" አዲስ የቡና ፕሮጀክት አምባሳደር ሆና ተመረጠች


     
        ኢትዮጵያዊቷ ሱፐር ሞዴል ገሊላ በቀለ በአለም አቀፍ ደረጃ በቡና ንግድ ታዋቂ በሆነው "ኔስፕሪሶ" አዲስ የቡና ፕሮጀክት አምባሳደር ሆና ተመረጠች ‹‹ቡቅላ ከ ኢትዮጵያ ›› የሚል ስያሜ የተሰጠው ይህ ፕሮጀክት ከአትዮጵያ ሁለት የቡና አብቃይ አካባቢዎች በቀጥታ ቡናን በመግዛት እና እሴት በመጨመር ለአለም ገበያ የሚያቀርብ ሲሆን ኢትዮጵያ የቡና መገኛ ምንጭ እንደሆነችም ለአለም ህዝብ እንደሚስተዋውቅ ተነግሯል፡፡
 

     ሱፐር ሞዴልዋም የድርጅቱን ድረ-ገጽ ጨምሮ ከሃምሳ በላይ በሆኑ ሃገራትም ፕሮጀክቱን የማስተዋወቅ ስራ እንደምትሰራ ለማወቅ ተችሏል፡፡  ኔስፕሪሶ በቡና እና ከቡና ጋር ተያያዙ ምርቶችን በማምረት ታዋቂ ሲሆን ለዚሁ  "ቡቅላ ከ ኢትዮጵያ " ለሚለው ፕሮጀክቱ ገሊላ በቀለን በአምባሳደርነት መምረጡን አስታውቋል፡፡


ስለ  ሱፐር ሞዴል ገሊላ በቀለ  ተጨማሪ  መረጃ  በዚህ ሊንክ ያገኛሉ  ➤➤➤ http://diretu.be/889733

No comments:

Post a Comment