Monday, February 24, 2014

ኢትዮጵያዊቷ ትርፌ ፀጋዬ የቶኪዮ ማራቶንን አሸነፈች


  ኢትዮጵያዊቷ አትሌት ትርፌ ፀጋዬ የቶኪዮ ማራቶንየቦታውን ክብረወሰን በመስበር ጭምር አሸነፈች ትርፌ 22223  በሆነ ሰዓት በመግባት ነው የሴቶችን የማራቶን ውድድር በበላይነት የፈፀመችው።  
  
  ትርፌን በመከተልሌላዋ ኢትዮጵያዊት አትሌት ብርሃኔ ዲባባ 22230 ሁለተኛ ስትወጣ ኬንያዊቷ ሉሲ ካቡ 22416 ሶስተኛ ወጥታለች፡፡ አትሌቷ ይህን ውድድር በቀዳሚነት ስታጠናቅቅ ለሶስተኛ ጊዜ ሲሆን ከሁለት ዓመት በፊት በሌላዋ ኢትዮጵያዊት አትሌት አፀደ ሀብታሙ ተይዞ የቆየውን ሪከርድም አሻሽላለች።

 የ29 አመቷ ትርፌ ጸጋዬ  2008 የፖርቶ ማራቶንን በማሸነፍ የጀመረች ሲሆን በፓሪስ እና በዱባይ ማራቶንም ቀዳሚ መሆን ችላለች፡፡ የራሷን ፈጣን ሰአትም በርቀቱ 2012 በበርሊን 22119 ማስመዝገቡዋ ይታወሳል፡፡
                                                                                 
   የኢትዮጵያዊያን እና ኬንያውያን የበላይነት በተስተዋለበት የቶኪዮ ማራቶን በወንዶቹ ምድብ 27 አመቱ ኬንያዊ ዲክሰን 2ሰአት አምስት ደቂቃ 42 ሰከንድ አሸናፊ ሆኖ ሲገባ ኢትዮጵያዊው ታደሰ ቶላ 20557 ሁለተኛ ሆኖአል፣ ሶስተኛ ሳሚ ኪትዋራ በመሆን ገብቷል፡፡ ሁለቱ የአፍሪካ ሀገራት በወንዶቹ ከአንደኛ እስከ ሰባተኛ በሴቶቹ ከአንደኛ እስከ አምስተኛ ያለውን ደረጃ ወስደዋል::                                               
                                                                    ምንጭ : -      www.iaaf.org                   

No comments:

Post a Comment