Thursday, February 27, 2014

በተለያዩ ሃገራት የሚገኙ ኢትዮጵያውያን እና ትውልደ ኢትዮጵያውያን በአዲስ አበባ ሆስፒታል ሊገነቡ ነው፡፡


  አለማቀፉ የኢትዮ- አሜሪካን ዶክተሮች ቡድን እና የአለም አቀፉ የኢትዮጵያውያን የህክምና ኢንተርይራይዝ በአዲስ አበባ የልህቀት ፣የትምህርት እና የምርምር መአከል የሆነ ሆስፒታል ለመገንባት የጋራ ስምምነት ላይ መድረሳቸው ተዘግቧል፡፡

     የሁለቱ ድርጅቶች የጋራ ጥምረት ከ250 በላይ ኢትዮጵያውያን እና ትውልደ ኢትዮጵያውያን የህክምና ባለሞያዎችን ያቀፈ ሲሆን ሌሎች ኢትዮጵያውያን የህክምና ባለሞያዎችንም የጥምረቱ አካል ለማድረግ ጥረት እያደረጉ መሆኑ ተዘግቧል፡፡

      የኢትዮጵያ መንግስትን ጨምሮ የተለያዩ አለም አቀፍ መንግስታዊ እና መንግስታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች እና ተቋማት ጥምረቱ ሊያስገነባ ላሰበው ሆስፒታል ድጋፍ እንሚያደርጉ ከወዲሁ መግለጻቸውንም ለማወቅ ተችሏል፡፡ ሊገነባ የታሰበው ሆስፒታል ጥራቱን የጠበቀ የህክምና አገልግሎት ፣የህክምና ትምህርት እና የሃገሪቱን የጤና ችግሮች ሊፈቱ የሚችሉ ጥናት እና የምርምር እንደሚያደርግም ተገልጿል፡፡

No comments:

Post a Comment