Friday, March 27, 2015

ከአርባ ምንጭ ወደ ጅቡቲ የተፈጥሮ ጋዝ ማስተላለፊያ ቱቦ ዝርጋታ ሊጀመር ነው፡፡

   
  የሚዘረጋው 1 231 ኪሎ ሜትር የተፈጥሮ ጋዝ ማስተላለፊያ ቧንቧ ከአርባምንጭ ተነስቶ በአዋሳ በድሬዳዋ አድርጎ በመጨረሻም ጁቡቲ ወደብ እንደሚደርስ ታውቋል። ይህን ስራ ለማስጀመር የሚስችል ፈንድ መገኘቱን እንዲሁም በኢትዮጵያ መንግስትና በጅቡቲ መካከል የስምምነት ውል መፈረሙንም የዘገበው ሰንደቅ ጋዜጣ ነው፡፡

   በአርባምንጭ የተገኘው የተፈጥሮ ጋዝ ክምችት በዓለም ከፍተኛ ክምችት ካላት ሩሲያ የሚበልጥ መሆኑ ተገልጿል። በአርባ ምንጭ የተገኘው የጋዝ ክምችት አዋጭነቱ ከካሉብ የተፈጥሮ ጋዝ ክምችት ጋር ፈጽሞ የማይገናኝና ለአበዳሪ ሀገራትም ከፍተኛ የሆነ መተማመን የፈጠረ በመሆኑ ለቱቦው ዝርጋታ ፈንድ እንዲለቀቅ አስችሏል።ኢትዮጵያም በዓለም ደረጃ ቁጥር አንድ የተፈጥሮ ጋዝ ክምችት ባለቤት የሚያደርጋት ከመሆኑም በላይ በቀጣይ በኢኮኖሚዋ ላይ አይነተኛ ድርሻ ይኖረዋል ሲል ጽፏል ጋዜጣው፡፡ 



    የጁቡቲ
መንግስት በበኩሉ የኢትዮጵያን የተፈጥሮ ጋዝ ለማከማቸት፣ ለማጣራት እና ለዓለም ገበያ ለማቅረብ 2 ነጥብ 6 ቢሊዮን ዳላር አዳዲስ ተርሚናሎች እየገነባ ነው። ጅቡቲ በዓመት ቢያንስ 10 ሚሊዮን ኪዩቢክ ሜትር የተፈጥሮ ጋዝ ከኢትዮጵያ ወደ ቻይና ለመላክ እየተሰናዳች መሆኑም ተጠቁሟል።  የአርባምንጩን የተፈጥሮ ጋዝ እያለማ የሚገኘው አፍሪካ ኦይል ኮርፖሬሽን የተባለ የካናዳ ኩባንያ ነው። ኩባንያው በነዳጅና በተፈጥሮ ጋዝ ፍለጋና ማምረት ላይ የተሰማራ ሲሆን፤ በአሁኑ ሰዓት ኩባንያው በኬኒያ፣ በኢትዮጵያ እና በፑንትላንድ ሥራዎቹን እያከናወነ ይገኛል፡፡

No comments:

Post a Comment