Monday, March 30, 2015

ኮሜዲያን ዳኒ ቁንጮ በ37 ዓመቱ አረፈ



   ከእናቱ / አስራት ሰቤ እና ከአባቱ ወልዴ ኪሮ 1970. አዲስ አበባ 4ኪሎ - ፊት በር ነበር ተወለደው፡፡ አንደኛ እና ሁለተኛ ደረጃ ትምህርቱን በዳግማዊ ምኒሊክ ተምሯል፡፡  በተለያዩ ክበባት ትያትርን ይሰራ የነበረው ዳኒ ቁንጮ ስዕልም ይሞክር  ነበር፡፡ ዳኒ ቁንጮ  በተለያዩ ክለቦች ሙዚቃን ያጫውት የነበረ ሲሆን በተለይ በኮሜዲ ስራዎቹ ነው የሚታወቀው፡፡ በዚህም በርካታ የኮሜዲ ስራዎቹን ለአድናቂዎቹ አበርክቷል፡፡ ኮሜዲያን ዳኒ ተክለሃይማኖት ሆስፒታል ለህክምና ከገባ በኋላ በሀኪሞች እርዳታ ቢደረግለትም ሊተርፍ አልቻለም፡፡ ባደረበት የኩላሊት ህመም በዚሁ የህክምና ተቋም ሲረዳ ቆይቶ መጋቢት 19 ቀን 2007ዓ.ም ማምሻውን ይህቺን ዓለም ተሰናብቷል፡፡

   ቀብሩም እሁድ መጋቢት 20 ቀን 2007ዓ.ም ከቀኑ 6፡00 ጉርድ ሾላ በሳሊተ ምህረት ቤተ ክርስቲያን ተፈፅሟል፡፡ ለኮሜዲያኑ ቤተሰቦች ፣ ወዳጅ ዘመዶች እና አድናቂዎች መፅናናትን እመኛለሁ፡፡

No comments:

Post a Comment