Wednesday, September 23, 2020

ዶ/ር ቴድሮስ አድሃኖም እና ትውልደ ኢትዮጵያዊው አቤል ተስፋዬ (ዘ ዊክንድ) የ2020 የዓለማችን ተፅዕኖ ፈጣሪዎች ዝርዝር ውስጥ ተካተቱ

የዘንድሮው ብሪጅ ሜከር አዋርድ አሸናፊ የሆኑት / ቴድሮስ አድሃኖም ከታይም መጽሔት 2020 የዓለማችን ተጽዕኖ ፈጣሪ 100 ሰዎች ዝርዝር ውስጥ ተካትተዋል።


የዓለም ጤና ድርጅት ዋና ዳይሬክተሩ / ቴድሮስ ከዓለማችን 100 ተፅዕኖ ፈጣሪ ሰዎች መካከል አንዱ ሆነው ሊመረጡ የቻሉት በተለይ ከኮቪድ-19 ወረርሽኝ ጋር በተያያዘ ሁሉም ሰው እኩል የጤና አገልግሎት ተደራሽነት እንዲያገኝ በያዙት ጠንካራ አቋም ነው ተብሏል። በተጨማሪም፣ በዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ የኢቦላ ወረርሽኝ ለመከላከል በተደረገው ጥረት የራሳቸውን አበርክቶ ማድረጋቸውም ተጠቃሽ ነው።


/ ቴድሮስ አድሃኖም 2020 ብሪጅ ሜከር አዋርድ ሽልማታቸውን በትላንትናው እለት የተቀበሉ ሲሆን ሽልማቱ ኮቪድ-19 ወረርሽኝን ለመከላከል ግንባር ቀደም ሆነው እያገለገሉ ላሉ የጤና ባለሙያዎች መታሰቢያ ይሁንልኝ ሲሉ የምስጋና መልእክታቸውን አስተላልፈዋል።

ሌላኛው ተፅዕኖ አሳዳሪ ትውልደ ኢትዮጵያዊ የካንዳ ዜግነት ያለው አቤል ተስፋዬ ( ዊክንድ) በአለም አቀፍ ደረጃ ተወዳጅነትን እያተረፈ የመጠ ድምፃዊ፣ ገጣሚ እና የሙዚቃ ፕሮዲውሰር ነው። አቤል ተስፋዬ ( ዊክንድ) 2020 በለቀቀው after hours በተሰኘ የሙዚቃ አልበም ተወዳጅነት ማግኘቱ የተነገረ ሲሆን በተለይ Blinding Lights ሙዚቃው 2020 በፖፕ ሙዚቃ ዘርፍ ተመራጪ መሆኑን መረጃዎቹ ያመለክታሉ።

                                   ምንጭ ፡- ኢ.ቢ.ሲ እና ኤፍ.ቢ.ሲ

No comments:

Post a Comment