Wednesday, February 26, 2020

የአዲስ አበባ ምክትል ከንቲባ ከቋሚ ሲኖዶስ ጋር ተወያዩ፡፡


የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ ኢንጂነር ታከለ ኡማ ትናንት የካቲት 17 ቀን 2012 . በቦሌ ክፍለ ከተማ በተለምዶ 24 በሚባለው አካባቢ ተፈጥሮ የነበረውን ችግር በተመለከተ ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቋሚ ሲኖዶስ ጋር ተወያይተው ችግሩ ከሦስት አካላት በተውጣጣ ኮሚቴ እንዲጣራ ተስማምተዋል።


ከሦስት አካላት ማለትም ከቤተ ክርስቲያን፣ ከአካባቢው ሽማግሌች እና ከመንግሥት አካል የተቋቋመው ኮሚቴ በዐሥር ቀናት ውስጥ ችግር የፈጠሩትን አካላት ማንነት፣ በቦታው የነበረውን ንዋያተ ቅድሳት ሁኔታ እንዲሁም ስለቦታው በዝርዝር አጥንቶ እንዲያቀርብ ስምምነት ላይ ደርሰዋል። በተፈጠረው ችግር ምክንያት ታስረው የነበሩ ክርስቲያኖች ክሳቸው ተቋርጦ በዛሬው ዕለት እንደሚፈቱም ከንቲባው ለቋሚ ሲኖዶስ አባላት ተናግረዋል።
                                                ምንጭ ፡- ማህበረቅዱሳን

No comments:

Post a Comment