Wednesday, November 4, 2015

በስለት ተወልዶ በስስት ያደገው …… ድምፃዊ ኪሮስ አለማየሁ


  በስለት ተወልዶ በስስት እንዳደገ ይነገርለታል፡፡ 1944. ትግራይ ክልል ፀአዳ አምባ ወረዳ ሰንደዳ ቀበሌ ነው የተወለደው ድምፃዊ ኪሮስ አለማየሁ፡፡ የቤተ ክህነት እውቀትን የቀሰመው ኪሮስ የአንደኛ እና ሁለተኛ ደረጃ ትምህርቱን በፍሬወይኒ ውቅሮ እና አፄ ዮሀንስ /ቤቶች ተከታትሏል፡፡ በመምህርነት እና በሀላፊነትም ሰርቷል፡፡ ከዚያም ከትግራይ ወደ አዲስ አበባ መጥቶ በራስ ትያትር ለአምስት አመታት ያህል የትግርኛ ሙዚቃዎችን ተጫውቷል፡፡ የመጀመሪያ አልበሙንም ራስ ትያትር እያለ ከሸበሌ ባንድ ጋር በመሆን ለአድናቂዎቹ አድርሷል፡፡
   

   1970ዎቹ አጋማሽ  በአዲስ  አበባ  ማዕከላዊ  እስር  ቤት  ታስሮ  የነበረው  ኪሮስ  አለማየሁ  በኪነቱ  ውስጥ  በነበረው  ቆይታ  በርከት  ያሉ  አስደሳች  አሳዛኝ እና አስቂኝ  ነገሮችን አሳልፏል፡፡ በስራዎቹም  ለትግሪኛ  ሙዚቃ  እድገት  ከፍተኛ  አስተዋፅኦ  አድርጓል፡፡ በተለያዩ   ርዕሰ  ጉዳዮች  ላይ  ያቀነቀነው  አንጋፋው  ድምፃዊ  ግጥም እና ዜማ  ይደርሳል፤ ዋሽንት  እና ክራር  የመሳሰሉትን  የሙዚቃ  መሳሪያዎችም  ይጫወታል፡፡

  
ድምፃዊ ኪሮስ አለማየሁ ነገሮችን እና ሁኔታዎችን አይቶ የመድረስ እና ከዜማ ጋር አዋህዶ የመጫወት ተሰጥኦው ላቅ ያለ ነው ይባልለታል፡፡ በአንድ ወቅትም ባለቤቱ አዲስ ሙሽራ ሆና ስትስቅ ስትጫወት እሷን በማየትአይቁንጅናየተሰኘውን ስራ እንደሰራው እና ከዚያም 1983. በካሴት እንዳሳተመው ይነገራል፡፡


ድምፃዊ ኪሮስ አለማየሁ በግሉ አምስት ከሌሎች ድምፃውያን ጋር ደግሞ ሁለት ያህል አልበሞችን ሰርቷል፡፡ ድምፃዊው በጥቅምት ወር 1986. ከዚህ አለም በሞት ተለይቷል፡፡ በስሙ ቤተ መፅሃፍት የተቋቋመለት ሲሆን ከመቀሌ ዩኒቨርስቲም የክብር ዶክትሬትን አግኝቷል፡፡ በቅርቡም የህይወት ታሪኩን በተመለከተ መፅሃፍ ተፅፎለታል፡፡ እሱ በህይወት ባይኖርም ስራዎቹ ህያው ናቸው እና ሁሌም ሲታወስ ይኖራል፡፡

No comments:

Post a Comment