Saturday, November 29, 2014

ፎርብስ የ2014 የዓለማችን ቢሊየነሮች እነኚህ ናቸው ብሎ ይፋ አድርጓል

    
     በትውልድ ኢትዮጵያዊና በዜግነት ሳውዲ አረቢያዊ የሆኑት ሼክ መሀመድ አሊ አላሙዲ 13. 6 ቢሊየን የአሜሪካ ዶላር ከዓለም 80 ደረጃ ላይ ተቀምጠዋል። የዓለማችን ቁጥር አንድ ቢሊየነርነትን ከአራት ዓመታት በኋላ አሜሪካዊው ቢል ጌትስ 82 . 4 ቢሊየን ዶላር ባለቤት በመሆን መልሶ ተረክቦታል።

   ከቢል ጌትስ በመቀጠልም የሜክሲኮ ዜግነት ያላቸው ካርሎስ ስሊም 79 .9 ቢሊየን ዶላር በሁለተኛ ደረጃ ላይ ተቀምጠዋል። አሜሪካዊው ዊገን ቡፌት 72 .7 ቢሊየን ዶላር ሶስተኛ ናቸው። የፌስቡክ መስራችና ባለቤት የሆነው ማርክ ዙከርበርግ 34 . 2 ቢሊየን ዶላር ከዓለም 14 ደረጃ ላይ ሲቀመጥ ከወጣቶች ደግሞ በሃብት መጠኑ 1 ሆኗል። 
  ናይጄሪያዊው ባለፀጋ አሊኮ ዳንጎቴ 20 ነጥብ 3 ቢሊዮን የአሜሪካምን ዶላር ሀብት ከአፍሪካ አንደኛ ከዓለም ደግሞ 37 ደረጃ ላይ ተቀምጠዋል። በአጠቃላይም ፎረብስ 1 ሺህ 645 ቢሊየነሮችን ዝርዝር ይፋ ያደረገ ሲሆን ከነዚህም 268 አዲስ መሆናቸው ታውቋል።  
                                                                                                                            ምንጭ ፡- ኤፍ.ቢ.ሲ

No comments:

Post a Comment