Monday, September 2, 2013

በሞሪሺየሱ ውድድር የኢትዮጵያ ታዳጊ አትሌቲክስ ቡድን 3ኛ በመሆን አጠናቀቀ


በሞሪሺየስ አስተናጋጅነት ሲካሄድ የቆየው 11ኛው የአፍሪካ ታዳጊ አትሌቲክስ ሻምፒዮና ትናንት ተጠናቀ። በውድድሩ 36 ሃገራት ሲካፈሉ ፥ ከእነዚህ ውስጥ 26 ሃገራት በሜዳልያ ሰንጠረዥ ውስጥ ገብተዋል። ውድድሩን ናይጀሪያ 9 የወርቅ ፣ 7 የብርና 8 የነሃስ በድምሩ 24 ሜዳልያዎችን በማግኘት በበላይነት ስታጠናቅቅ ፥ ደቡብ አፍሪካ ደግሞ 7 የወርቅ ፣ 9 የብርና 8 የነሃስ በድምሩ በ24 ሜዳልያዎች ሁለተኛ ደረጃን ይዛ አጠናቃለች።


  ኢትዮጵያ 7 የወርቅ ፣ 7 የብርና 8 የነሃስ በድምሩ 22 ሜዳልያዎችን በማግኘት ውድድሩን 3ኛ በመሆን አጠናቃለች። ኢትዮጵያ በ2011 በተካሄደ ተመሳሳይ ውድድር  17 ሜዳልያዎችን ያስመዘገበች ሲሆን ፥ የዘንድሮው ውድድር የተሻለ ውጤት የተመዘገበበት ነው። የናይጀሪያ እና የጋና መገናኛ ብዙሃን ኢትዮጵያ በመካከለኛ ርቀት ያስመዘገብችው ውጤት አበረታች መሆኑን ዘግበዋል።

                                                                                                             ምንጭ ፡-    ኤፍ ቢ ሲ
      


No comments:

Post a Comment