Thursday, February 14, 2013

አንጋፋው ድምፃዊ ታምራት ሞላ ሥርዓተ ቀብር የካቲት 4 ቀን 2005 ዓ.ም. በመንበረ ጸባዖት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል ተፈጸመ፡፡

 ከዓመታት በፊት ባደረበት የደም ካንሰር ሕመም ምክንያት በአገር ውስጥና በውጭ አገሮች ከፍተኛ ሕክምና ሲከታተል የቆየው ድምፃዊ ታምራት በተወለደ 69 አመቱ ከዚህ አለም በሞት ተለይቷል፡፡ትምህርቱን አቋርጦ የክብር ዘበኛ የልጅ ወታደር በመሆን
 ሙዚቃን የጀመረው ታምራት፣ 1955 . በምድር ጦር ኦርኬስትራ ባልደረባ በመሆን እስከ 1983 . ድረስ በድምፃዊነትና በዜማ ደራሲነት አገልግሏል፡፡ከመንግሥት ለውጥ በኋላ በሀገር ፍቅር ቴአትር የሠራው ታምራት፣ በግማሽ ምእት ዓመት
የሙዚቃ ሕይወቱ  በርካታ ዘፈኖችን ያቀረበ ሲሆን፣ ከእነሱም መካከል ‹‹ታምሜ ተኝቼ ትናንትና ሌሊት›› ‹‹ዘወትር ብርቅነሽ›› ‹‹ሰበቡ ለምን ትይኛለሽ›› ይገኙበታል፡፡


አንጋፋው ድምፃዊ ታምራት ሞላ  1936-2005
  አርቲስት ታምራት ሞላ በ1936 ዓ.ም ከአባቱ ከፊት አውራሪ ሞላ ዘለለውና ከእናቱ ከወይዘሮ አበራሽ የኔነህ  በጎንደር ከተማ ተወለደ። በ1953 ዓ.ም ከጎንደር ወደ አዲስ አበባ ከአጎቱ ጋር በመምጣት በክቡር ዘበኛ የልጅ ወታደር በመሆን የሙዚቃውን አለም አሃዱ ብሎ ጀመረ። በ1955 ዓ.ም አብዛኛውን የሙዚቃ ህይወቱን ያሳለፈበትን የምድር ጦር ሰራዊትን የተቀላቀለው አርቲስት ታምራት ሃገራዊ  ማህበራዊ እና ፍቅርን መሰረት ያደረጉ ሙዚቃዎችን ከመጫወቱ ባለፈ ድራማ እና ቲያትርን ምክንያት አድርጎ መድረክ ላይ መቆም መቻሉን ታሪኩ ያስረዳል።     በተለይም ትግላችን በሚል ቲያትር በመሪ ተዋናይነት ከመጫወቱም ባለፈ  የበርካታ ዜማዎች ድርሰትን ቀምሮ ለህዝብ አቅርቧል። በሃገር ፍቅር ቲያትር ቤት ለረጅም ጊዜያት በድምጻዊነት ያገለገለው አርቲስት ታምራት  ከ50 አመታት በላይ ባስቆጠረው የሙዚቃ ህይወቱ ከአድማጭ ጆሮ የማይጠፉና የማይረሱ ሙዚቃዎችን ተጫውቷል። አርቲስት ታምራት በተለያዩ ሃገራዊ ተሳትፎዎች ላይ ኪነ ጥበቡን በመወከል በሙያው ሃገሩን አገልግሏል። በተለይም በኢትዮኤርትራ ጦርነት ወቅት ከሙያ አጋሮቹ ጋር በመሆን  በአውደ ውጊያው ተገኝቶ የጦር ሰራዊቱን ሲያበረታታ ነበር።  የቀብር ስነ ስርዓቱ ትላንት  10 ሰአት በመንበረ ፀባኦት ቅድስት ስላሴ ካቴድራል ቤተሰቦቹ  ወዳጅ ዘመዶቹ  የሙያ አጋሮቹ እና አድናቂዎቹ በተገኙበት ተፈጸሟል። 
ድምፃዊው ታምራት ሞላ ባለትዳርና የሁለት ሴቶችና ሦስት ወንዶች አባት ነበር፡፡    



   






No comments:

Post a Comment