Sunday, September 22, 2013

ኢትዮጵያዊቷ ብሩክታይት ደገፋ ለ12 ዓመታት የቆየውን የሲድኒን ማራቶን ሪከርድ በመስበር አሸነፈች

  ኢትዮጵያዊቷ አትሌት ብሩክታይት ደገፋ በሲድኒ 12 ዓመታት ሳይሰበር የቆየውን የሴቶች የማራቶን ክብረወሰን በመስበር  አሸነፈች።

   በዛሬው እለት በሲድኒ የተካሄደው ይህ 42.2 ኪሎ ሜትር ውድድር ቀደም ሲል .. 2001 በአውስትራሊያዊቷ ክሪሻና ስታንቶን  2 ሰዓት 38 ደቂቃ 11 ሰከድ ተይዞ የነበረ ሲሆን ብሩክታይት 2 ሰዓት 32 ደቂቃ 45 ሰከንድ በሆነ ግዜ ነውየቦታውን ክብረወሰን  በማሻሻል ጭምር ማሸነፍ የቻለችው።
  በሌላ በኩል የሴቶች ግማሽ ማራቶኑን  ውድድር ላውራ ጀምስ የተባለችው አውስትራሊያዊት 1 ሰዓት 18 ደቂቃ 36 ሰከንድ በመግባት በአንደኛነት አጠናቃለች  በተመሳሳይ በተካሄደው  የወንዶች የማራቶን የሩጫ ውድድር ኬንያዊው ዊሊ ኪቦር ድል የቀናው ሲሆን ኪቦር 2 ሰዓት 13 ደቂቃ 48 ሰከንድ አንደኛ ሆኖ ጨርሷል።  
                                    ምንጭ:  9news

No comments:

Post a Comment