Friday, February 20, 2015

ገንዘቤ ዲባባ በ5ሺህ ሜትር ክብረ ወሰን ሰበረች

  
   ገንዘቤ ዲባባ በስቶኮልም በተካሄደ የ5ሺህ ሜትር የቤት ውስጥ ውድድር 14፡18.86 በመግባት የርቀቱን ክብረ ወሰን የግሏ አድርጋለች፡፡ የ5ሺህ ሜትር የቤት ውስጥ ውድድር ክብረ ወሰን 14፡24፡37 በሆነ ሰዓት በመሰረት ደፋር ተይዞ የነበረ ነው፡፡ ገንዘቤ ክብረ ወሰኑን የሰበረችው የመሰረትን ሰዓት በ5 ሰከንድ በማሻሻል ነው፡፡

  ብርቱካን ፈንቴ እና ብርቱካን አዳሙ15፡22፡56 እና 15፡34.15 በሆነ ሰዓት ገንዘቤን ተከትለው ገብተዋል፡፡ ገንዘቤ ባሳለፍነው የጎርጎሮሳውያኑ 2014 በ15 ቀናት ውስጥ ሶስት ክብረ ወሰኖችን መስበሯ ይታወሳል፡፡ገንዘቤ ዲባባ በቤት ውስጥ ውድድሮች ፈርጥ እየሆነች መምጣቷን ዘገባው አትቷል፡፡
                                                          ምንጭ፡-ራነርስ ወርልድ

No comments:

Post a Comment