Thursday, April 27, 2017

ኢትዮጵያዊው አስትሮ ፊዚስት ዶ/ር ለገሰ ወትሮ ከዚህ ዓለም በሞት ተለዩ፡፡


   ዶ/ ለገሰ በቀድሞ አጠራር በአሩሲ ክፍለ ሀገር ስሬ ወረዳ 1942 . ነበር የተወለዱት፡፡ የአንደኛ እና ሁለተኛ ደረጃ ትምህርታቸውን በተወለዱበት አካባቢ ተከታትለዋል፡፡ የመጀመሪያ ዲግሪያቸውን ከቀዳማዊ ኃይለስላሴ (የአሁኑ አዲስ አበባ  ዩንቨርሲቲ) ያገኙት / ለገሰ ሁለተኛ ዲግሪያቸውንም በዚሁ ዩኒቨርስቲ  በፊዚክስ ትምህርት አጠናቀዋል፡፡  በውጭ ሀገር ከሼፊልድ ዩናይትድ  በፊዚክስ ሁለተኛ ዲግሪያቸውን ያገኙ ሲሆን ሶስተኛ ዲግሪያቸውን ደግሞ ከከሎምቢያ ስቴት ዩንቨርሲቲ በአስትሮኖሚ/አስትሮፊዚክስ አግኝተዋል፡፡


 በንፋስ ስልክ አጠቃላይ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ለአራት ዓመታት ያስተማሩት / ለገሰ 40 ዓመታት ያህል በመምህርነትና በተመራማሪነት በአዲስ አበባ ዩንቨርሲቲ አገልግለዋል፡፡ዶ/ ለገሰ ወትሮ  አስትሮኖሚ/አስትሮ- ፊዚክስ ምርምር የሚታወቁ እና አዳዲስ ፅንሰ - ሀሳቦችን ያበረከቱ ታላቅ ሰው ነበሩ ብሏል የአዲስ አበባ ዩንቨርሲቲ መግለጫ፡፡


  ዶ/ ለገሰ ወትሮ በኤፍ ኤም አዲስ 97.1 “የህዋ ሳይንስ” የተሰኘ ፕሮግራም በማዘጋጀት ለአድማጮች ስለ ህዋ ሳይንስ ሰፊ ግንዛቤ ይሰጡም ነበር፡፡ በተወለዱ 67 ዓመታቸው ያረፉት / ለገሰ የአንድ ወንድና የሁለት ሴት ልጆች አባት ነበሩ፡፡ የዶ/ ለገሰ ወትሮ ስርዓተ ቀብር ሚያዝያ 20/2009 ከቀኑ 900 ሰዓት በጴጥሮስ መካነ መቃብር ይፈጸማል ሲል አዲስ አበባ ዩንቨርሲቲ አስታውቋል፡፡
       ለቤተሰቦቻቸው እና ወዳጅ ዘመዶቻቸው መፅናናትን እንመኛለን!!!

No comments:

Post a Comment