Thursday, August 11, 2016

"ዘማቹ ጓዴ" …………… ፀሃዬ ዮሀንስ


    በ197 . መጨረሻ ላይ በአምባሣደር ቲያትር ቤት ተቀጥሮ መድረክ ላይ የተጫወተው "ማንበብ እና መፃፍ" የሚል ስራውን ነበር፡፡ ብዙዎች ይህንን የፀሃዬ ዮሀንስ የመጀመሪያ ስራ አድርገው ይቆጥሩታል ይሁንና እሱ ግን ከዚህ በፊት ብርሃን ኢትዮጵያ ትምህርት ቤት እያለ የእድገት በህብረት መዝሙሮችን ይጫወት ነበር፡፡ ለአብነትም "ዘማቹ ጓዴ" የተሠኘውን መጥቀስ ይቻላል፡፡ "ማንበብ እና መፃፍ" የተሠኘው ዘፈን ግጥም ደራሲ ዳምጠው ሲሆን ዜማው የራሱ የፀሃዬ ዮሀንስ ነው ፡፡ የሀሣቡ መነሻ ደግሞ በጊዜው በአምባሣደር ትያትር ቤት በርከት ያሉ ያልተማሩ ሰዎች መኖር ነበር፡፡ ዘፈኑ ከመሠተረ ትምሀርት አዋጁ ቀደም ብሎ የተሠራ ቢሆንም ከአዋጁ በኋላ ግን ድምፃዊ ፀሃዬ ከፍተኛ ታዋቂነትን አግኝቶበታል፡፡


   ከአምባሣደር ትያትር ቤት ወደ ራስ ቲያትርም ተዛውሮ 1973 -1983 . ድረስ ያገለገለው ፀሃዬ ዮሀንስ በዚህ ቆይታው በርከት ያሉ ዘፈኖችን በካሴት አሣትሞ ለህዝብ አድርሷል፡፡ የመጀመሪያ ካሴቱ "ተይ ሙኒት" ሲሆን ፍንጭቷ፣ ብቸኝነቴን፣ ማን እንደ ሀገር፣ ያላንቺማ እረ ስንቱን ተባለ እንዴ ለትንሽ እና ሳቂልኝ እያለ ቀጥሎ በቅርቡም "የኔታ" የተሠኘ አልበሙን ጀባ ብሎናል፡፡

  
   በ1975 . አካባቢ "ፍንጭቷ" የተሠኘውን ስራውን በካሴት ሲያሣትም ብዙዎቹ የዘፈን ግጥም ድርሰቶች የጋዜጠኛ ልዑል አማራ ነበሩ፡፡ በተለይ "ፍንጭቷ" የተሰኘው ዘፈን ደራሲው የፃፈውፍንጭቱበማለት ራሱን ፀሃዬ ዮሀንስ መነሻ በማድረግ ነበር የሰራው፡፡ ፀሃዬ ግንፍንጭቱየሚለው ወደ "ፍንጭቷ" በመቀየር ተጫውቶታል ፡፡ ይህን ዘፈን በጣም እንደሚወደው ፀሃዬ ዮሀንስ በአንድ ወቅት ገልፆ ነበር፡፡ ለጎዳና ተዳዳሪዎችየጥቁር አበቦችየሚል ስራ የተጫወተው ፀሃዬ ዮሀንስ እናቱን በሞት እንዳጣም ለእናቱምትክ አልባ እናቴየተሰኘ ስራ ተጫውቷል፡፡ ለድምፃዊ ፀሀዬ ዮሀንስ እድሜ እና ጤና በመመኘት ቀሪውን እናንተ ጨምሩበት……. 

No comments:

Post a Comment