Tuesday, May 26, 2015

አርቲስት ሻምበል መኮንን መርሻ ከዚህ አለም በሞት ተለዩ



   አንጋፋው የፖሊስ ኦርኬስትራ ሙዚቀኛ የነበሩት ሻምበል መኮንን መርሻ ትላንት ከዚህ አለም በሞት ተለይተዋል።አርቲስቱ በ1950ዎቹ መባቻ የፖሊስ ኦርኬስትራን ተቀላቅለው በሙዚቃው ከግማሽ ምዕተ አመት በላይ አሳልፈዋል፡፡ አርቲስቱ የታዋቂ ድምፃውያንን ሙዚቃ በመድረክ በማጀብ እና በካሴት በማቀነባበር ለሀገራችን የሙዚቃ እድገት የበኩላቸውን ድርሻ ተወጥተዋል፡፡


    ጥላሁን ገሰሰ ፣ አለማየሁ እሸቴ ፣ ሂሩት በቀለ ፣ ዘሪቱ ጌታሁን እና ታደለ በቀለን የመሳሰሉ አንጋፋ ድምፃውያንን በትራንፔት በማጀብ ተወዳጅነትን አትርፈዋል፡፡ ሻምበል መኮንን መርሻ በመድረክ ላይ ከሚያሳዩት ድንቅ የትራንፔት አጨዋወት ባለፈ ኦሮምኛ ሙዚቃን በመጫወትም በ1950ዎቹ ስመ ገናና ድምፃዊ ነበሩ፡፡

   
   አንጋፋው የፖሊስ ኦርኬስትራ ሙዚቀኛ ሻምበል መኮንን መርሻ የቀብር ስነ ስርዓት ዛሬ በቂርቆስ ቤተክርስቲያን ቤተሰቦቻቸው ፣ ወዳጅ ዘመዶቻቸው እና አድናቂዎቻቸው በተገኙበት ተፈፅሟል፡፡      

No comments:

Post a Comment