Tuesday, May 2, 2017

ደስታ፣ ሳቅ እና ጨዋታ የእሳቸው መለያ ናቸው ... ተዋናይት አስካለ አመነሸዋ


 “ለእኔ ራሱ ግርም ይለኛል ጭንቅላቴ ካሴት ማለት ነው አንዴ የተነገረኝን /የያዝኩትን/ ቶሎ አልረሳም በቃ ካሴት በሉኝእያሉ ጨዋታቸውን ሲያዥጎደጉዱት አፍ ያስከፍታሉ፡፡
   
  የብሄራዊ ቲያትሯ መሪ ተዋናይ አርቲስት አስካለ አመነሸዋ ከትወናው አለም እስከተገለሉበት ጊዜ ድረስሂሩት አባቷ ማን ነው ጨምሮ 40 በላይ ቲያትሮች ላይ ተሳትፈዋል፡፡ የድል አጥቢያ አርበኛ፣ ስነ-ስቅለት፣ አሸርቶስ ንጉስ፣ ቂመኛው ባህታዊ፣ ስራሽ ያውጣሽ፣ ታርቱፍ፣ ማንም ሰው፣ ደህና ሁኚ አራዳ፣ ደመ መራራ፣ ንግስት ሳባ፣ አንድ አመት ካንድ ቀን፣ በህይወት ዙሪያ፣ ቴዎድሮስ፣ ስስታሙ መንጠቆ፣ አስቴር፣ ጎንደሬው /ማሪያም፣ አወናባጅ ደብተራ፣ ምኞቴ፣ የሺ፣ እኝ ብዬ መጣሁ፣ ለሰው ሞት አነሰው፣ ኦቴሎ፣ የበጋ ሌሊት ራዕይ፣ የከተማው ባላገር፣ ጠያቂ እና የአዛውንቶች ክበብን ለአብነት መጥቀስ ይቻላል፡፡ በአንጋፋው ጋዜጠኛ እና ደራሲ ነጋሽ /ማሪያም የተደረሰው የአዛውንቶች ክበብ የመጨረሻ ስራቸው እንደሆነም ይናገራሉ፡፡
  

   በኢላላ ኢብሳ የተደረሰ በኢትዮጵያ የመጀመሪያው ነጭ እና ጥቁር ፊልም ነው፡፡ ፊልሙ በሃገር ፊልምና ማስታወቂያ ስራ አማካኝነት በሆሊዩድ ነው የተሰራው፡፡በ35 ሚሊ ሜትር የተሰራው ይህ ፊልም በህይወት ውጣ ውረድ ውስጥ ስለምትኳትን አንዲስ ሴት እና በልጇ ህይወት ላይ ትኩረቱን ያደረገ ነው፡፡ በዚህ ፊልም ላይ ከተወኑት አንዷ አርቲስት አስካለ አመንሸዋ ሲሆኑ በመሪ ተዋናይነት የፅዲቱን የቡና ቤት ገፀ ባህሪይ ተላብሰው ተውነዋል፡፡ ቀደም ባለው ጊዜ ከንጉሰ ነገስቱ የወርቅ የአንገት ሀብል፣  “የሂሩት አባቷ ማን ነው” 50 አመትን ምክንያት በማድረግ ዋንጫ እና የገንዘብ ሽልማት ተበርክቶላቸዋል፡፡ ባለፈው አመት ደግሞ “የጉማ ሽልማት” ዓመታዊ ክብረ በዓል በኢትዮጵያ የፊልም ጥበብ የ2008ዓ.ም ምርጥ የእድሜ ዘመን ተሸላሚ ሆነዋል፡፡


 
  የኋላው ከሌለ የለም የፊቱ ….. አይደል ያለው ቴዲ አፍሮ በዘፈኑ፡፡ እኛም ቀደምቶቻችንን እናስብ፤ እነሱንም እንጠይቅ፣ እንመርምር ብዙ ቁምነገሮችንም እናገኛለንና…….

No comments:

Post a Comment